ፋርስ

ከውክፔዲያ

ፋርስ እስላማዊ ሪፐብሊክ

የፋርስ ሰንደቅ ዓላማ የፋርስ አርማ
ሰንደቅ ዓላማ አርማ
ብሔራዊ መዝሙር مهر خاوران
የፋርስመገኛ
የፋርስመገኛ
ዋና ከተማ ቴህራን
ብሔራዊ ቋንቋዎች ፋርስኛ
መንግሥት
መሪ
ፕሬዝዳንት
ምክትል ፕሬዝዳንት
እስላማዊ ሪፐብሊክ
ዓሊ ኽሃመነኢ
ሓስሳን ሮኡሃኒ
ዐስሃቅ ጃሃንጊሪ
የመሬት ስፋት
አጠቃላይ (ካሬ ኪ.ሜ.)
ውሀ (%)
 
1,648,195 (17ኛ)
0.7
የሕዝብ ብዛት
የ2016 እ.ኤ.አ. ግምት
 
82,800,000 (18ኛ)
ገንዘብ ፋርስ ሪኣል ﷼
ሰዓት ክልል UTC +3:30
የስልክ መግቢያ +98
ከፍተኛ ደረጃ ከባቢ .ir
ایران.


ፋርስ አገር (ፋርስኛ፦ ایران /ኢራን/) ወይም የኢራን ኢስላማዊ ሬፑብሊክ (جمهوری اسلامی ایرا /ጆምሁሪ-የ ኤስላሚ-የ ኢራን) በእስያ ውስጥ የሚገኝ አገር ነው። ዋና ከተማው ቴህራን ነው።

ስም[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ለኗሪዎቹ የሀገር ስም ከጥንት ጀምሮ ኢራን ሲሆን ከአገር ውጭ እንደ ፋርስ ወይም በመሰለ ስያሜ ይታወቅ ነበር።

1927 ዓም ሻህ (ንጉስ) ሬዛ ሻህ ሀገሩ በውጭ አገራት ዘንድ «ኢራን» በመባል እንዲታወቅ ጠየቀ። (በዚህም ወቅት ያህል ደግሞ በመንግሥታት ማኅበር መሃል የኢትዮጵያ ስያሜ በ1923 ዓም ከ«አቢሲኒያ» ተቀየረ፤ የታይላንድም በ1932 ዓም ከ«ሲያም» ተቀየረ።)

1951 ዓም ግን ልጁ ሻህ ሙሃመድ ሬዛ ፓሕላቪ ሁለቱ ስያሜዎች (ኢራን እና ፋርስ) አንድላይ በመለዋወጥ ትክክለኛ እንደ ተቆጠሩ አዋጀ።

ኢራን[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ዞራስተር ባዘጋጀው በአቨስታ ዘንድ ሕዝቡ «አይርያ» (አርያኖች) ይባላሉ፤ መጀመርያ አገር ቤታቸው «አይርያነም ቫይጃህ» ሲባል ይህ በአራስ ወንዝ አካባቢ እንደ ተገኘ ይታመናል።[1] ከዚህ መጀመርያ አገር በኋላ የተከተሉት አገራት በአፍጋኒስታንና በፋርስ አካባቢ ሲገኙ ይህም አውራጃ በጥንት «አሪያና» እና «አሪያ» ይባል ነበር። ሄሮዶቶስ 480 ዓክልበ.ግ. የሜዶን ብሔር ድሮ ስም «አሪዮይ» እንደ ነበር መሰከረ፤ የፋርስ አሓይመኒድ ነገስታት እንደ ፩ ዳርዮስ ብሔራቸውን «አሪያ» አሉት። ከሳሳኒድ ሥርወ መንግሥት ጀምሮ (218 ዓም) በመካከለኛ ፋርስኛ የሀገሩ ኗሪ ስም «ኤራን» ወይም «ኢራን» ሆኗል።

ፋርስ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

መጀመርያ በ800 ዓክልበ. ግድም ፓርሱማሽ ወይም ፓርሱዓሽ፣ ፓርሱ፣ ፓርሳ የሚባል አነስተኛ የአርያኖች ወገን በኡርሚያህ ሐይቅ ዳርቻ ተመዘገቡ፤ እነዚህም ከትንሽ በኋላ ወደ ቀድሞው ኤላም ሔደው ስማቸውን ለዛሬው ፋርስ ክፍላገር ሰጡ፤ የአሓይመኒድ ሥርወ መንግሥት መሠረቱ። ቋንቋቸውንም እስካሁን «ፋርሲ» (ፋርስኛ) ይሉታል። ስማችውና አገራቸው ከዚሁ በግሪክኛ «ፐርሲስ»፣ በሮማይስጥ «ፐርሲያ»፣ በዕብራይስጥ «ፐረስ»፣ በአማርኛም «ፋርስ» በመባል ታውቋል።

  1. ^ አቨስታ ፋርጋርድ ፩ (እንግሊዝኛ) ነጥብ ፫