ሜዶን

ከውክፔዲያ
የሜዶን መንግሥት ስፋት (ቢጫ) በ600 ዓክልበ. ግድም

ሜዶን በጥንታዊ እስያ (ፋርስ) የተገኘ መንግሥት ነበር። ስማቸው በጥንታዊ ፋርስኛ እንዲሁም በአሦርኛና በዕብራይስጥ «ማዳይ» ሲሆን በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ከያፌት ልጅ ማዴ (ማዳይ) የተወለደ ሕዝብ ናቸው። «ሜዶን» የሚለው ስያሜ ከግሪክ ነው። በ620 ዓክልበ. ሜዶን የአሦርን መንግሥት አሸነፈ፤ ለጥቂት ዘመን ሰፊ መንግስት ነበረው። በ558 ዓክልበ. ግን ሜዶን ለፋርስ ንጉሥ ቂሮስ ወደቀ።