አርጎብኛ ከደቡባዊ ሴሜቲክ ቋንቋወች አንዱ ነው። በአንድ ወገን ከአማርኛ በሌላ ወገን ከሐረሪኛ ጋር ተመሳሳይ ቅርጽ ያለው ቋንቋ ሲሆን የሚነገረውም በሸዋና ሐረር ተንሰራፍተው በሚኖሩት የአርጎባ ብሄረሰብ ነው።