ሶማሊላንድ
ከWikipedia
ሶማሊላንድ እውቅና ያልተሰጠው በስራው ግን እንደ አንድ ልዑላዊ ሃገር የሚንቀሳቀስ በአፍሪካ ቀንድ በሰሜን ምስራቅ ሶማሌ የሚገኝ አካል ነው። በ1983፥ የሶማሊላንድ ህዝብ ነጻነቱን አውጆ ከሶማሌ 18 ክፍለ ሃገራት 5ቱን አካቶ ይዟል። ይህም በጅቡቲ በኢትዮጵያ በቀድሞው የጣልያን ሶማሊላንድና በአዴን ጎልፍ የሚካለለውን 137,600 ኪሎሜትር ካሬ የሚሸፍነውን ቦታ ከሞላ ጎደል ይሸፍናል። የሶማሊላንድ ዋና ከተማ ሃርጌሳ ነው።
እውቅና ባያገኝም አካሉ ሳይዋዥቅ እንደ መንግስት እየሰራ ይገኛል። በመስከረም 18 ቀን 1998 በተደረገው የከተሞች የሊቀመንበርና የህዝብ ተወካዮች ምርጫ ኡዱብ ፓርቲ ሲያሸንፍ በተለያዩ ታዛቢዋ ትክክለኛና ነጻ ምርጫ እንደ ነበር ዘገባ ቀርቧል። ይህም ሶማሊላንድ ላቀረበችው የእውቅናው ጥያቄ ድጋፍ ይሰጣል የሚሉ ወገኖች አሉ።
|
||||||||||||||||||||||||||||