ኬንያ
|
የኬንያ ሪፐብሊክ |
||||||
|---|---|---|---|---|---|---|
|
||||||
| ብሔራዊ መዝሙር: «ኤ ሙንጉ ንጉቩ ዬቱ» (ስዋሂሊ) |
||||||
|
ኬንያ በአረንጓዴ ቀለም
|
||||||
| ዋና ከተማ | ናይሮቢ |
|||||
| ብሔራዊ ቋንቋዎች | እንግሊዝኛ እና ስዋሂሊ | |||||
| መንግሥት ፕሬዝዳንት ምክትል ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር |
የከፊል ፕሬዝዳንታዊ ሪፐብሊክ ሙአይ ኪባኪ ካሎንዞ ሙስዮካ ራይላ ኦዲንጋ |
|||||
| ዋና ቀናት ታኅሣሥ ፪ ቀን ፲፱፻፶፮ ዓ.ም. (ዲሴምበር 12, 1963) ታኅሣሥ ፫ ቀን ፲፱፻፶፯ ዓ.ም. (ዲሴምበር 12, 1964) |
ነፃነት ከብሪታንያ ሪፐብሊክ ታወጀ |
|||||
| የመሬት ስፋት አጠቃላይ (ካሬ ኪ.ሜ.) ውሀ (%) |
580,367 (47ኛ) 2.3 |
|||||
| የሕዝብ ብዛት የ2012 እ.ኤ.አ. ግምት የነሐሴ ፳፻፩ ዓ.ም. ቆጠራ |
43,013,341 (31ኛ) 38,610,097 |
|||||
| ገንዘብ | የኬንያ ሺሊንግ | |||||
| የሰዓት ክልል | UTC +3 | |||||
| የስልክ መግቢያ | +254 | |||||
| ከፍተኛ ደረጃ ከባቢ | .ke | |||||
የኬንያ ሪፐብሊክ በምስራቅ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በሰሜን ከኢትዮጵያ፣ በሰሜን-ምስራቅ ከሶማሊያ፣ በደቡብ ከታንዛኒያ፣ በምስራቅ ከዩጋንዳ፣ በስሜን-ምዕራብ ከደቡብ ሱዳን፣ በደቡብ-ምስራቅ ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር ድንበር ትጋራለች። የኬንያ ስም የመጣው በአፍሪካ በከፍታ ሁለተኛ ከሆነው ከማውንት ኬንያ ተራራ ነው።
አውሮፓውያን አካባቢውን ማሰስ የጀመሩት ከ፲፱ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ሲሆን የብሪታንያ መንግሥት የምሥራቅ አፍሪካ ፕሮቴክቶሬትን በ1895 እ.ኤ.አ. አቋቁሟል። ይህ ፕሮቴክቶሬት በ1920 እ.ኤ.አ. የኬንያ ግዛት ተብሎ ተሰይሟል። ነፃ የኬንያ ሪፐብሊክ በዲሴምበር 1963 እ.ኤ.አ. ታወጀ።
በኦገስት 2010 እ.ኤ.አ. በተካሄደ ውሳኔ ሕዝብ (referendum) መሠረት ከብሪታንያ የተወረሰው ሕገ መንግሥት በአዲስ ሕገ መንግሥት ተለውጧል። በአሁኑ ጊዜ ኬንያ በ፵፯ ካውንቲዎች (የአስተዳደር ክፍሎች) ተዋቅራለች። እነዚህ ካውንቲዎች በሕዝብ በተመረጡ ሰዎች የሚስተዳደሩ ሲሆን በናይሮቢ ከሚገኘው ማዕከላዊ መንግሥት በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ።
የኬንያ ዋና ከተማ እና ትልቋ ከተማ ናይሮቢ ናት። የኬንያ ኢኮኖሚ በምሥራቅና መካከለኛው አፍሪቃ በጂ.ዲ.ፒ. (GDP) ትልቁ ነው። ግብርና በአገሪቱ ትልቅ የሥራ ዘርፍ ሲሆን ከኤክስፖርቶች መካከል ሻይ፣ ቡና እና ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ አበባዎች ይገኛሉ።
|
||||||||||||||||||||||||||||