ሞሮኮ

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

المملكة المغربية
አል ማምላካህ አል ማግርቢያ
የሞሮኮ መንግሥት

የሞሮኮ ሰንደቅ ዓላማ የሞሮኮ አርማ
ሰንደቅ ዓላማ አርማ
የሞሮኮመገኛ
ዋና ከተማ ራባት
ብሔራዊ ቋንቋዎች ዓረብኛ
መንግሥት
ንጉሥ
ጠቅላይ ሚኒስትር
 
ንጉሥ ሙሐመድ ሳድሳዊ
አባስ ኤል ፋሲ
የመሬት ስፋት
አጠቃላይ (ካሬ ኪ.ሜ.)
 
446,550 (56ኛ)
ገንዘብ ድርሃም
ሰዓት ክልል UTC +0
የስልክ መግቢያ +212


ሞሮኮ (አማርኛ፡ መግሪብ) በሰሜን-ምዕራብ አፍሪቃ የምትገኝና በሕገ-መንግሥታዊ የዘውድ ሥርዓት የምትተዳደር የ፴፪ ሚሊዮን ሕዝብ አገር ናት። መግሪብ በምዕራብ ድንበሯ የአትላንቲክ ውቅያኖስ፤ በሰሜን የሜድትራኒያን ባሕር፤በምሥራቅ አልጄሪያ እና በደቡብ ምዕራባዊ ሣህራ ታዋስናለች። የመግሪብ ርዕሰ ከተማ በአገሪቱ በስተ ምዕራብ የምትገኘውና በሕዝብ ብዛት ሦስተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ራባት (አማርኛ፡ ርባጥ]] ስትሆን የንግድና የኢንዱስትሪ ማዕከል እንዲሁም የአገሪቷ ታላቅ የባሕር ወደብ የሚገኝባት የካዛብላንካ ከተማ እና ጥንታዊቷ ማራኬሽ (አማርኛ፡ ምራክሽ) ሌሎቹ ትላልቅ ከተሞች ናቸው።