ገብስ (ሮማይስጥ፦ Hordeum vulgare) የእህል አይነት ነው። እንዲሁም እህሉ ከዘሮቹ የመጣው የሣር ተክል አይነት ነው። ከጥንት ጀምሮ ለሰዎች ምግብና ለእንስሶች መኖ ይጠቅማል፤ ከዚህም በላይ ብቅል በማድረግ ቢራና ሌላ መጠት ለመሥራት ይጠቀማል። ከእህሉም የወጣው ዱቄት እንደ ዳቦ ሊሠራ ይችላል። ይህ እህል ለዕድሜ እጅግ ጤነኛ ምግብ መሆኑ ይታወቃል።