ጎርጎርያን ካሌንዳር

ከውክፔዲያ
የሮማው ፓፓ ግሪጎሪ 8ኛ መቃብር ላይ ፓፓው የካሌንደሩን መጽደቅ አስመልክቶ ሲደሰት የሚያሳይ ቅርጽ

የጎርጎርያን ካለንዳር ወይም በሌላ ስሙ የምዕራቡ ካሌንዳር በአለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያለው የቀናት አቆጣጠር ዘዴ ነው። ካሌንደሩን ያስተዋወቀው የሮማው ፓፓ ግሪጎሪ ፰ኛ ነበር። ካሌንደሩ በህዳር 24፣ 1582 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ) የጎርጎርያን ካሌንደር ተብሎ ተሰየመ፣ በአዋጅም ጸና። የአዲሱ ካሌንደር መነሻ ምክንያት የጁሊያን ካሌንደር በአንድ አመት ውስጥ 365.25 ቀንናቶች አሉ ብሎ ያስቀመጠው እምነቱ በ11 ደቂቃወች ከዕውነተኛው የአመት ርዝመት አንሶ መገኘቱ ነበር። ስለዚህም የጁሊያን ካሌንደር ከተሰራ ጀምሮ ፓፓው እስከ ቀየረው ድረስ የተጠራቀመው ስህተት 10ቀን ወጣው። ይህ የ10 ቀን ለውጥ የካቶሊክ ቤ/ክርስቲያናንን የፋሲካ በዓል ስላዛባ ካሌንደሩ መስተካከሉ የግድ ሆነ።