ፍሬንድስ (ተከታታይ ፊልም)

ከውክፔዲያ
ፍሬንድስ ተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማ

ፍሬንድስ (እንግሊዝኛ: Friends) የአሜሪካ ተወላጅ በሆኑት ዴቪድ ክሬን (እንግሊዝኛ: David Crane)እና ማርታ ኩፍማን (እንግሊዝኛ: Marta Kauffman) የተፈጠረ የቴሌቪዥን ድራማ ነው። ይህ ተከታታይ ፊልም በአየርላይ የዋለው በኤንቢሲ ከእ.አ.አ. ሴፕቴምበር 22፣ 1994 እስከ ሜይ 6፣ 2004 ነበር። ፊልሙ በኒው ዮርክ ከተማ ማንሃታን ውስጥ ስለሚኖሩ ጓደኞች ህይወት ዙሪያ የሚያጠነጥን ሲሆን በይዘቱ በአስቂኝ ንግግሮች እና ድርጊቶች የተሞላ መሆኑ አስቂኝ ፊልም ያሰኘዋል።