ፍቅር
ከWikipedia
ፍቅር ከልብ (ልቦና) ውስጥ የሚወጣ ጠንካራ የመውደድ ስሜት ነው። ፍቅር በብዙ አስተሳስቦች በኩል ልዩ ልዩ ትርጉሞች አሉት። ለምሳሌ «የሕይወት መዓዛ» ተብሏል።
[ለማስተካከል] ፍቅር በብሉይ ኪዳን
«ፍቅር እንደ ሞት የበረታች ናት» - መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን 8፡6
በአይሁድም በክርስትናም በአንዳንድም ሌሎች ሃይማኖቶች በሚከብረው በብሉይ ኪዳን ውስጥ፣ ፍቅረ ቢጽ በኦሪት ዘሌዋውያን 19፡18 ይታዘዛል፦ «ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ»... እንደገና ዘዳግም 10፡19፦ «እናንተ በግብፅ አገር ስደተኞች ነበራችሁና ስለዚህ ስደተኛውን ውደዱ።»
በመጽሐፈ ምሳሌ ደግሞ፦ «የጎመን ወጥ በፍቅር መብላት የሰባ ፍሪዳን ጥል ባለበት ዘንድ ከመብላት ይሻላል።» - (15፡17)
[ለማስተካከል] ፍቅር በአዲስ ኪዳን
ክርስቲያኖች የሚቀበሉት አዲስ ኪዳን ስለ ፍቅር በርካታ ተጨማሪ ትምህርት ይጠቅሳል። ለምሳሌም፦
- «ወዳጆች ሆይ፣ ፍቅር ከእግዚአብሔር ስለ ሆነ፣ የሚወደውም ሁሉ ከእግዚአብሔር ስለ ተወለደ እግዚአብሔርንም ስለሚያውቅ፣ እርስ በርሳችን እንዋደድ።» -- 1 ዮሐንስ መልእክት 4፡7
- «እግዚአብሔር ፍቅር ነው፣ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል፡ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል።» -- 1 ዮሐንስ መልእክት 4፡16
- «ማንም፦ እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል?» -- 1 ዮሐንስ መልእክት 4፡20
- «እግዚአብሔርን ስንወድ ትእዛዛቱንም ስናደርግ፡ የእግዚአብሔርን ልጆች እንድንወድ በዚህ እናውቃለን።» -- 1 ዮሐንስ መልእክት 5፡2