ፓሪሲ

ከውክፔዲያ
የፓሪሲ ወርቅ እስታቴር
የፓሪሲ ወርቅ እስታቴር

ፓሪሲሴን ወንዝ አጠገብ (በአሁኑ ፈረንሳይ) በጥንት ቢያንስ ከ3ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ. ጀምሮ እስከ ሮሜ መንግሥት ድረስ የኖረ የኬልቶች ብሔር ነበር።

60 ዓክልበ. ከሌላ ጎሣ ሱዌሲዮኔስ ጋራ በአለቃው ዌርኪንገቶሪክስ መሪነት የዩሊዩስ ቄሣርን ወረራ ተቃወሙ። ዩሊዩስ ቄሣርም እንደ ጻፈ ዋና ከተማቸው በሮማውያን ሥር ሉቴቲያ (የአሁኑም ፓሪስ) ሆነ። ከሮማውያን ቀድሞ ይህ ሥፍራ «ሉኮቶኪያ» ይባል ነበር።

ሌላ ፓሪሲ የሚባል ኬልቲክ ብሔር በአሁኑ እንግላንድ ይገኝ ነበር። የዚህ ብሔር ቅርንጫፍ መሆናቸው በሊቃውንት ተከራካሪ ነው።