ስልጤኛ

ከውክፔዲያ
(ከስልጢኛ የተዛወረ)

ስልጢኛኢትዮጵያ የሚነገር ቋንቋ ሲሆን የሴማዊ ቋንቋዎች አባል ነው። የቋንቋው መጠሪያ ስልጢኛ በመባል ሲጠራ ስያሜውን ያገኘውም ከብሄረሰቡ ስም “ስልጤ” ከሚለው ነው።”ስልጤ” በዞኑ በሚገኙ በዋነኛነት አምስት ማኅበረሰቦች ማለትም ስልጢ:መልጋ:ሁልባረግ:አዘርነት በርበሬና አልቾውሪሮ የጋራ መጠሪያ ነው። በማኅበረሰቦቹ በታሪክ: በማኅበራዊ ኑሮ :በባህል: በቋንቋና በሀይማኖት እንዲሁ ተመሳሳይ ናቸው የስያሜውን መነሻ በተመለከተ የተለያዩ መረጃዎች ያሉ ሲሆን ስያሜውን ያገኘው ከሀጂ አሊዬ 5ተኛ ልጅ ከሆኑት ገን- ስልጤ አልያም ሱልጣኔት ከሚለው አረብ ኢስላማዊ መንግስት ጥንታዊነት እንዲሁም ነባር ኢስላማዊ መንግስታትና ማኅበረሰቦች የታሪክ ወራሽነትንበማሰብ ነው የሚለው በስፋት ይገለፃል::☞ስልጢኛ ቋንቋ ከሴማዊያን ቤተሰቦች ይመደባል .. ቋንቋው በስፋት ከሀረሪኛና የዛይ ቋንቋ ጋር በጣም ሲመሳሰል በበርካታ የቃላት ትርጉዋሜ ደረጃ ከአረብኛ: አማርኛ ትግርኛ አርጎቢኛና ኦሮምኛ ጋርም ይገናኛል:: ሌላው ስልጤ የምትጠራባቸው ተጨማሪ ስም “እስላም“ ተብሎሲጠራ ፡ ቋንቋውም”እስላምኛ” በመባል በደቡብ ክፍል እስከ ዛሬ ይታወቃል ።በሰሜኑ የሀገራችን ህብረተሰብ ዘንድ ስልጤ ‘ ጉራጌ` ተብሎ የሚታወቅ ቢሆንም ስልጤ የራሱን ዞን ከመሰረተ ጀምሮ ይህ መጠሪያ ስሙ ላይመለስ ቀርቶዎል።ስልጢኛ ከ6ዐ ዓመት በፊት የአረብኛ ፊደልን በመጠቀም ለጽሑፍ የዋለ ቋንቋ ቢሆንም ከ1967 ዓ/ም ጀምሮ ልዩ ልዩ አዋጆች እና የመሰረተ ትምህርት ማስተማሪያ መጽሐፍት የሳባ ፊደልን በመጠቀም በቋንቋው ተተርጉመዋል፡፡ ከ1987 ዓ/ም ጀምሮ የ1ኛ ደረጃ የመጀመሪያ ሣይክል የመማሪያ መጽሐፍት በቋንቋው ተዘጋጅተዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የትምህርት ቋንቋ ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡ እንደዚሁም የሣባ ፊደልን በመጠቀም የመማሪያ መጽሐፍት፣ የስልጢኛ መዝገበ ቃላት፣ የስልጤ ሕዝብ ታሪክ እና ሌሎች መጽሀፍቶች በቋንቋው ተጽፈው አገልግሎት እየሠጡ መሆናቸው ቋንቋው በማደግ ላይ ያለ ስለመሆኑ የሚገልፁ እውነታዎች ናቸው፡፡