አርጎባ (ወረዳ)

ከውክፔዲያ
(ከአርጎባ(ወረዳ) የተዛወረ)

አርጎባ የሚለዉ ስያሚ «በወቅቱ የነበሩ አፄዎች አረብ ገባ ብለዉ የአርጎባ ማህበረሰብን መጠርያ ከአርጎባ ጋር ያያልዙታል። ይህ የብሄረሰቡ ትክክለኛ መጠርያ ሳይሆን ሊሉ የፈለጉት ዉጫዊ ናቸዉ ለማለት ነዉ። አርጎባዎች  መቶ በመቶ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ናቸዉ። በእርሻ በንግድና በሽመና ይተዳደራሉ። በኢትዮጵያ የነበሩት የአፄ መንግስታት የእስልምና ሃይማኖትን የማይቀበሉ ስለነበሩ ወይም ደግሞ እንደሌላዉ ሃይማኖት እኩል የማያራምዱ ስለነበሩ መጤ ናቸዉ የዉች ሰዎች ናቸዉ በማለት አረብ ገባ {አርጎባ }የሚል ስያሚ ሰጥዋቸዉ። ትክክለኛዉ ታሪክ ግን አርጎባ በኢትዮጵያ ይኖር የነበረ ጥንታዊ ህዝብ ነዉ

በተለይ በ 13ኛዉ ክፍለ ዘመን የይፋት ወላስማ ሥርወ መንግስት ንግድን መስርቶ ይኖር የነበረ በኢትዮጵያ የመጀመርያዉን እስላማዊ መንግስት የመሰረተ ከዝያም በሁለተናዉ ሂጅራ በነብዩ መሃመድ የእስልምና እምነት ተከታዮች ከቁርሾች ጋር በነበረዉ ግጭት ወደ ኢትዮጵያ የገቡ አረቦችን ተቀብሎ ያስተናገደ ሃይማኖታቸዉንም የተቀበለ የኢትዮጵያ የመጀመርያዉ የሙስሊም ማህበረሰብ ነዉ ማለት ይቻላል::

ዛሬ አርጎቦች በደቡብ እስከ ባሌ በምስራቅ እስከ ሐርር፣ አፋር ሰሜን ሸዋ ትግራይ ድረስ ይገኛሉ::




አርጎባ (ወረዳ) አቀማመጥ

አርጎባ (ወረዳ)
አርጎባ (ወረዳ)



ማጣቀሻ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]