ክሻትሪያ

ከውክፔዲያ
ጃይን ሃይማኖት አስተማሪ ማሃዊራ (607-535 ዓክልበ.) የክሻትርያ መደብ አባል ነበረ።

ክሻትሪያህንዳውያን ኅብረተሠብ በተለያዩ 4 መደባት የሚከፋፈልበት አንዱ የህብረተሰባዊ ክፍል (ካስት) ነው። በዚህ አከፋፈል ዘዴ የወታደሮችና የገዢዎች ክፍል እሱ ነው። ክሻትሪያ ከብራህሚን (ቄሳውንትና አስተማሮች) በታችና ከቫይስያ (ነጋዴዎች) እንዲሁም ከሹድራ (ሠራተኞች፣ አገልጋዮች) በላይ ሆኖ ይቆጠራል።

በመጀመርያ በጥንት ይህ ደረጃ በሰው ችሎታ፣ ተግባርና ጸባይ ምክንያት ሊገኝ የቻላ ሲሆን፣ በዘመናት ላይ ግን የተወረሰ ማዕረግ (በዘር የሚዛወር) ብቻ ሆነ። በአንዳንድ ወቅት ደግሞ የክሻትሪያ (መኳንንት) ክፍል ከብራህሚኖች (ቄሳውንት) ክፍል ይልቅ ላየኛነቱን ይይዝ ነበር። ብራህሚኖችም በኋላ የበለጡት ከትግል በኋላ እንደ ሆነ ይታመናል።

የቃሉ ሥር በሕንዳዊ-ኢራናዊ ቋንቋዎች ቤተሠብ «*ክሺ» 'መግዛት' ሲሆን ለዚሁ ብዙ የተዛመዱ ቃሎች (እንደ ሳንስክሪት «ክሻትራ» 'ግዛት') ይኖራሉ። በጥንታዊ ፋርስኛ በኩል «ሕሻጥራ» ማለት 'ሃይል፣ መንግሥት' ነበረ፤ የ«ሕሻያጢያ» ትርጉም የፋርስ ንጉሠ ነገስት ሆኖ ከዚህ በዘመናዊ ፋርስኛ ንጉሥ ሻህ ይባላል። በአማርኛ፣ ቼዝ (ሰንጠረዥ) የሚባል ጨዋታ ስም ከዚህ የመጣ ነው። በተጨማሪ በፋርስ ታሪክ የጠቅላይ ግዛት ወይም አገረ ገዥ ማዕረግ «ሕሻጥራ-ፓዋ» (የግዛት ጠባቂ) በኋላ «ሳትራፕ» ሆነ። ሌሎች ቃላት በታይላንድኛ «ካሳት» 'ንጉስ' በመላይኛም «ሳትሪያ» 'ጀግና' ከ«ክሻትሪያ» የተነሡ ናቸው።

ሕንዱ ሃይማኖት መጻሕፍት የክሻትሪያ ታሪክና ሚና ይወሰናል። በርግ ዌዳ ዘንድ እያንዳንዱ መደብ ወይም 'ዋርና' ከፈጣሪ አምላክ (ብራህማ) ሰውነት ተነሥቶ የክሻትሪያ መደብ የተነሣ ከትከሾቹና ከክንዶቹ ነበረ። በሌላ ትርጉም ከጥፋት ውሃ ያመለጠው ሕግ ሰጪ ማኑአርያን ኅብረተሰብ ባከፋፈለበት ጊዜ ክሻትርያዎቹ ማርሻል አርትስ (እንደ ጁዶካራቴ ወዘተርፈ) የተማሩት ነበሩ። እያንዳንዱ ዋርና (ካስት) በልዩ ቀለም ሲመለከት የክሻትሪያ ቀለም ቀይ ሆነ።

በሌሎች መጻሕፍት መሠረት፣ በዙሪያ የተገኙ ሕዝቦች በድሮ እንደ ክሻትርያ ቢቆጠሩም፣ የብራህሚኖችን ሃይማኖት ግን በደንብ ስላልጠበቁ፣ በኋላ ከክሻትርያው ሁኔታ ወደቁ። ከነዚህም፣ ሳካዎቹ (የእስኩቴስ ሰዎች)፣ ያዋኖቹ (የግሪክ ሰዎች)፣ ፓህላቮቹ (የፋርስ ሰዎች)፣ ድራዊዶቹ (የደቡብ ሕንድ ጥቁሮች) እና የቻይና ሰዎች ሁላቸው በቀድሞ ክሻትሪያዎች ነበሩ። ዛሬ ግን አብዛኞቹ ክሻትርያዎች በህንድ አገር የአርያኖች (ነጮች) ሕዝብ አባላት ናቸው። ከሕንድ አገር ውጭ ከክሻትርያ የተወለዱ ዘሮች በተለይ በኢንዶኔዥያ፣ በቬትናምና በሽሪ ላንካ ይገኛሉ። የዛሬው ክሻትርያ ቤተሠቦች በጠቅላላው ከመደባቸው ውጭ አይጋቡም።

ከሕንድ አገር ስርወ ነገስታት በቀር፣ በታሪክ ውስጥ ሌሎች የተገነኑ ክሻትርያዎች የቡድሃ ሃይማኖት አስተማሪ ጎታማ ቡድሃ እና የጃይን ሃይማኖት አስተማሪ ማሃዊራ ናቸው። በቡድሂስትና በጃይን ሃይማኖቶች ግን የ'ክሻትርያ' ትርጉም «ጦረኛ» ሳይሆን «ገበሬ»፣ «ባለመሬት» ብቻ ነው። በህንድ ሃይማኖት በኩል፣ ዋና አማልክታቸው ራማ እና ክሪሽና ክሻትርያዎች ይባላሉ።