ልዩ አንጻራዊነት

ከውክፔዲያ

ልዩ አንጻራዊነትአልበርት አይንስታይን የተጻፈ፣ በ፲፱፻፭ ዓ.ም. ለህትመት የበቃ የተፈጥሮ ህግጋት ጥናት መጽሃፍና ርዕዮተ አለም ነው። ይህን ርዕዮተ አለም እንዲያዳብር እና እንዲያስፋፋ አይንስታይንን ከገፋፋው ዋናው ምክንያት በጊዜው የነበረው አጥጋቢ ያልሆነ የኮረንቲና ማግኔት ማዕብል ጽንሰ ሃሳብ ነበር። በአይንስታይን አስተያያት፣ በጊዜው የነበረው ርዕዮት የኮረንቲማግኔት ማዕበሉን ከሚከታተሉ ሰወች/መሳሪያወች መርጦ ለአንዱ የሚያደላ እንደሆነ ተገነዘበ። ሆኖም ግን ጋሊልዮ የተባለው የጣሊያን ሳይንቲስት ከ300 አመታት በፊት የአንጻራዊነት ርዕዮትን ሲገነባ በማናቸውም የተፈጥሮ ሂደቶች ውስጥ የሚከሰትን ኩነት ሁሉም ተመልካች እኩል እይታ እንዳለውና አንዱ ተመልካች ከሌሎቹ በተለየ መልኩ «ትክክል» አስተያየት እንደሌለው አስተምሯል። ስለሆነም አይንስታይን ከላይ የተጠቀሰውን አድሏዊ አስተያየት ለማስተካከል ነበር ልዩ አንጻራዊነትን የጻፈው።

ሀሳቡም የአይዛክ ኒውተን ፍፁማዊ እረፍት (Absolute Rest )እና ፍፁማዊ ጊዜን (Absolute time) የሚቃረን ሲሆን በ ኒውተን ሀሳብ ላይ የተመረኮዘው ዩኒቨርስ ላይ በማንኛውም ቦታ ላይ በፈለግን ፍጥነት ብንጓዝ ለሁሉም አካል ጊዜ በእኩል ፍጥነት የሚጓዝ የሚጓዝ ነው የሚል ሲሆን ማንኛውም አካል በፈለገው ፍጥነት መጓዝ በበቂ ግፊት (Force) መጓዝ ይችላል የሚለውን ሀሳብ የሚቃረን ነው። የ Absolute rest ሀሳብ በ "Michelson " እና "Morley" ጥናት ወይም ሙከራ ይህ ሀሳብ ፍፁም ስህተት መሆኑን የሚያሳይ ሲሆን እንዲሁም የብርሃን ፍጥነት የፍጥነት ሁሉ መጨረሻ መሆኑን ያሳያል። እንደዚሁም በተለያዩ ጥናቶች እንደተረጋገጠው የአንድ አካል ፍጥነት በጨመረ ቁጥር እርሱ ጋር ያለው ጊዜ እያዘገመ ወይም እየዘገየ የሚሄድ መሆኑን ተረጋግጧል ።

በአጠቃላይ ልዩ አንፃራዊነት በ አይዛክ ኒውተን ትክክል ናቸው ያላቸውን የ Absolute time እና የ Absolute spaceን ሀሳብ የሚቃወም ሲሆን

1, የብርሃን ፍጥነት (300000km/s) የፍጥነት ሁሉ የበላይ መሆኑን

2,በዩኒቨርስአችን ውስጥ በፍጥነት የሚሄዱ አካላት የሚቆጠሩት ጊዜ በእረፍት ላይ ካሉት የሚበልጥ መሆኑን

3, ለብርሃን ፍጥነት በቀረበ ፎጥነት የሚጓዝ አካል እረፍት ላይ ከነበረበት ትልቀት የሚያጥር መሆኑን ያሳያል