ልዩ አንጻራዊነት
ከውክፔዲያ
ልዩ አንጻራዊነት በአልበርት አይንስታይን የተጻፈ፣ በ፲፱፻፭ ዓ.ም. ለህትመት የበቃ የተፈጥሮ ህግጋት ጥናት መጽሃፍና ርዕዮተ አለም ነው። ይህን ርዕዮተ አለም እንዲያዳብር እና እንዲያስፋፋ አይንስታይንን ከገፋፋው ዋናው ምክንያት በጊዜው የነበረው አጥጋቢ ያልሆነ የኮረንቲና ማግኔት ማዕብል ጽንሰ ሃሳብ ነበር። በአይንስታይን አስተያያት፣ በጊዜው የነበረው ርዕዮት የኮረንቲና ማግኔት ማዕበሉን ከሚከታተሉ ሰወች/መሳሪያወች መርጦ ለአንዱ የሚያደላ እንደሆነ ተገነዘበ። ሆኖም ግን ጋሊልዮ የተባለው የጣሊያን ሳይንቲስት ከ300 አመታት በፊት የአንጻራዊነት ርዕዮትን ሲገነባ በማናቸውም የተፈጥሮ ሂደቶች ውስጥ የሚከሰትን ኩነት ሁሉም ተመልካች እኩል እይታ እንዳለውና አንዱ ተመልካች ከሌሎቹ በተለየ መልኩ «ትክክል» አስተያየት እንደሌለው አስተምሯል። ስለሆነም አይንስታይን ከላይ የተጠቀሰውን አድሏዊ አስተያየት ለማስተካከል ነበር ልዩ አንጻራዊነትን የጻፈው።
| ጅምር! (ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። እርስዎ ሊያስፋፉት ይችላሉ!) |