ሙቀት

ከውክፔዲያ
ይህ የፀሓይ ገጽታን ቀረብ ብለን ስናየው ምን እንደሚመስል የሚያሳይ ፎቶ ነው። አብዛኛው መሬት ላይ የሚገኝ ህይወት ያለው ነገር በሙሉ ሃይሉን የሚያገኘው በፀሐይሙቀትና ብርሃን የተነሳ ነው።

ሙቀትተፈጥሮ ህግ ጥናት ከአንድ ቁስ ወደ ሌላ ቁስ ያለምንም ስራ አቅም ሲተላለፍ ማለት ነው። ባጭሩ ለማስረዳት፣ አንድ ሰው ትልቅ ድንጋይ ወደላይ ቢያነሳ በዲንጋዩ ላይ ስራ ሰርቷአል ምክንያቱም የሰውየው ጉልበትና ድንጋዩ የተጓዘበት አቅጣጫ አንድ አይነት ስለሆነ። እንግዲህ ድንጋዩ ከፍተኛ ቦታ ላይ ሰለሆነ ያለው ቢለቀቅ ስራ ሊሰራ ይችላል፤ ይህም አቅም ከሰውየው ወደ ድንጋዩ ስራ ተላልፏል ማለት ነው። ለአቅሙ መተላለፍ ስራ ስለተሰራ ትልልፉ ሙቀት አይባልም። ባንጻሩ ድንጋዩን ፀሐይ ላይ ብንተወው እየጋለ ይሄዳል። ይህ ግለት ውሃ እላዩ ላይ ጠብ ቢልበት በማትነን በውሃ ላይ ስራ መስራት ይችላል። ይህ የሚያሳየው አቅም ከፀሐይ ወደ ድንጋዩ መተላለፉን ነው። ነገር ግን ፀሐዩዋ ድንጋዩን ስላላንቀሳቀሰችው ስራ አልሰራችበትም። ስራ ሳይሰራ የሚደረገው የአቅም ልውውጥ ሙቀት ይባላል።