ሰሃራ በረሃ
ሠሃራ በረሃ (አረብኛ፦ الصحراء الكبرى አል-ኩብራ ወይም ታላቁ በረሃ ማለት ነው።[1]) የአለማችን ሰፊው ሞቃት በረሃ ነው። በዚህም ስፋቱ ከ9,400,000 ካሬ ኪ.ሜ. (3,630,000 ካሬ ማይል) በላይ ነው። በረሃው የሚሸፍነው አብዘሀኛውን የሰሜን አፍሪካ ክፍል ሲሆን በስፋቱም ከአውሮፓ ወይም ከአሜሪካ ጋር ይወዳደራል። ከዚህ በረሃ የሚሰፋው ብቸኛው አንታርክቲካ ሲሆን ይህም የሆነው በዝቅተኛ የዝናብ መጠን ነው። የሰሀራ በረሃ የሚያካልለው የሜዲትራኒያን ጠረፍ ጨምሮ ቀይ ባሕርን እስከአትላንቲክ ውቅያኖስ ጠረፍ ድረስ ያለውን ነው። በስተደቡብ የሳር ምድር እና የቁጥቋጦ ምድር የሆነውን ከበረሃው ጋር በሚያገናኘው የሳህል መቀነት ያዋስነዋል።
አንዳንዶቹ የአሸዋ ክምሮች እስከ 180 ሜትር (590 ጫማ) ከፍታ አላቸው።[2]
[ለማስተካከል] የአየር ሁኔታ ታሪክ
የሰሃራ በረሃ ባለፉት ጥቂት መቶ ሺህ አመታት ሲለዋወጥ የቆየ የአየር ሁኔታ ነበረው። በቀዝቃዛው የበረዶ ዘመን ክፍል (glacial period) ጊዜ በረሃው ከዚህም በላይ ሰፊ ነበር። በዚህ ዘመን መጨረሻ (ከ8000 ዓ.ዓ. እስከ 6000 ዓ.ዓ.) አካባቢ በርከት ያለ የዝናብ መጠን ተመዝግቦ ነበር።
[ለማስተካከል] በረዶ
በፌብርዋሪ 18, 1979 በአብዘሀኛው ደቡባዊ አልጀሪያ በረዶ የቀላቀለ ዝናብ ጥሎ ነበር። በዚህ ዕለት ለግማሽ ሰዓት ያህል የቆየ የበረዶ ነጎድጓድ የነበረ ሲሆን ከሰዓታት በኋላ በረዶው ጠፍቷል። ይህ ዜና በተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ለመጀመሪያ ጊዜ በህይወት የምናስታውሰው ዝናብ ሰሃራ በረሃ ላይ በሚል ርዕስ ሊወጣ ችሏል።
[ለማስተካከል] የውጭ ማያያዣዎች
- ^ http://online.ectaco.co.uk/main.jsp?do=e-services-dictionaries-word_translate1&status=translate&lang1=23&lang2=ar&source_id=2119140 |title=English-Arabic online dictionary |publisher=Online.ectaco.co.uk |date=2006-12-28 |accessdate=2010-06-12
- ^ Arthur N. Strahler and Alan H. Strahler. (1987) Modern Physical Geography–Third Edition. New York: John Wiley & Sons. Page 347