አለማየሁ እሸቴ

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አለማየሁ እሸቴ

አለማየሁ እሸቴ ታዋቂ ኢትዮጵያዊ ዘፋኝ ሲሆን ብዙ ዘመናዊ የሙዚቃ ስራዎችን በማቅረብ ይታወቃል።

[ለማስተካከል] የህይወት ታሪክ

አለማየሁ እሸቴ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአርበኞች ት/ቤት ተከታትሎ ባደረበት ጥልቅ የሙዚቃ ስሜትና ባለው ግሩም ተሰጥኦ ተገፋፍቶ ድምጻዊነቱን በፖሊስ ሠራዊት ሙዚቃ ክፍል ጀመረ። ብዙዎቹ የአለማየሁ ዘፈኖች ከስሜት በሚያፈልቃቸው ዜማዎች ዘመናዊነት የሚታይባቸውና ከውጭ ሀገር ዘፈኖች ጋር ይመሳሰላሉ።[1]

[ለማስተካከል] የሥራዎች ዝርዝርና ውጤት

ቀደም ሲል «እዬዬ»፣ «ማሪኝ ብዬሻለሁ» በተሰኙት ዜማዎቹና «ስቀሽ አታስቂኝ»፣ «ማን ይሆን ትልቅ ሰው»፣ «እንደ አሞራ ክንፍ አውጥቼ ልብረራ» በሚላቸው ዘፈኖቹ በብዙዎች ዘንድ የታወቀ አርቲስት ነው። ለሚስቱና ለልጆቹ ማቆላመጫ «ውዷ ባለቤቴ!» የምትል ዜማ ተጫውቷል።[1]

አለማየሁ እስካሁን ድረስ ከ፷፪ በላይ ዜማዎቹ በሸክላ ተቀርጸው ፲፭ ሺህ ያህሉ ተሽጠውለታል።[1]

[ለማስተካከል] ማጣቀሻ

  1. ^ ናሽናል ቢብሊዮግራፊ ቡድን፣ የአንጋፋ አርቲስቶች መዝገበ የሕይወት ታሪክ፣ መጋቢት ፳፻፣ ገጽ 30-31
የኔ መሣርያዎች

Variants
Actions
የማውጫ ቁልፎች
ጠቃሚ መሣሪያዎች
በሌሎች ቋንቋዎች