ካቡል

ከውክፔዲያ

ካቡልአፍጋኒስታን ዋና ከተማ ነው።

ካቡል

የሚኖርበት የህዝብ ቁጥር 2,206,300 ሆኖ ይገመታል። ከተማው 34°31′ ሰሜን ኬክሮስ እና 69°12′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።

የካቡል ዕድሜ ቢያንስ 3,000 አመት ነው። ጥንታዊ ስሙ በሳንስክሪት ኩብሃ፣ በግሪክኛ ኮፌን ነበረ። ለፋርሶችና ለግሪኩ ፕቶለሚ ካቡራ ተብሎ ታወቀ። የቻይና ሊቅ ሿን ጻንግ (7ኛ ክፍለ ዘመን የኖረ) ደግሞ ካውፉ ይለዋል።