ዋንዛ

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዋንዛ (Cordia Africana) በኢትዮጵያ እንዲሁም በአፍሪካ ሁሉ የሚበቅል ግዙፍ ዛፍ ነው። ፍሬው ሲበስል በጣም ጣፋጭ ነው። የፍሬው ይዘት ከላይ ለስላሳና ሙሽሽ የሚል ሲሆን መሃሉ ላይ ግን የማይቆረጠም፣ ምናልባትም ያጠቃላይ ፍሬውን 3/5ኛ የያዘ ፍሬ አለ። [1]

የዋንዛ ተጨማሪ ጥቅሞች [ለማስተካከል]

ሌሎች አትክልቶችን፣ ለምሳሌ እንደ ቡና ያሉትን፣ ከፀሐይ ለመከላከል ይረዳል። ጥላ መከታም ይሆናል።

ቀፎን ዛፉ ላይ በማስቀመጥ፣ ንቦችን ለማርባት በጣም አይነተኛ ዛፍ ነው፤ ምክንያቱም የዛፉ አበቦች መዓዛቸው መልካም ሲሆን መልካቸውም ዓይን ይስባል (በተለይ የንቦችን አይን)።

ግንዱም ለተለያዩ የቤት እቃ መስሪያነት ይጠቅማል፣ ለቅርጻቅጽም እንዲሁ።

ለዋንዛ ተስማሚ የሆነ አየር ጠባይና መሬት [ለማስተካከል]

ዋንዛ ከደጋ በስተቀር ቆላወይና ደጋ ተስማሚው ናቸው።

የዋንዛ አስተዳደግና እንክብካቤ [ለማስተካከል]

በጣም በፍጥነት ያድጋል። እስክ 30 ሜትር ይደርሳል።

  1. ^ http://ethiopia.limbo13.com/index.php/wanza/