ዕውነተኛ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
«ይህ ገጽ ከእንግሊዝኛው በቀጥታ የተቀዳ ነው። ቀስ በቀስ ይተረጎማል በማለት ነው።»


ዕውነተኛ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያንቤጂንግ ቻይና1909 ዓ.ም. የተመሠረተ ነፃ ቤተ ክርስቲያን ነው። በ6 አህጉር ላይ 1.5 ሚሊዮን የሚያሕሉ ምዕመናን አሉት። ቤተ ክርስቲያኑ በቻይና የወጣ ከጰንጤ እንቅስቃሴ የተነሣ ነው።

ይህ ቤተ ክርስቲያን ግን የሥላሴ ጽንሰ ሐሳብ አይቀበልምና «የኢየሱስ ስም ትምሀርት» ተከታዮች ናቸው።

ማውጫ

[ለማስተካከል] አምስቱ ዋና ትምህርቶች

የዕውነተኛ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን 5 አይነተኛ ትምሀርቶች እንደሚከተል ናቸው፦

[ለማስተካከል] መንፈስ ቅዱስ

«መንግሥተ ሰማያትን የመውረሳችን ዋስትና መንፈስ ቅዱስ በመቀበል ነውና እሱም ባልታወቀ ልሳናት በመናገር ይገለጻል።» መንግስተ ሰማያት የመውረሳችህን ዋና ነገር ገታ እየሱስ እንደግል አዳናችን በመቀበል ነው

[ለማስተካከል] ጥምቀት

«የውሃ ጥምቀትኃጥአት ስርየት ለተሐድሶ የሆነው ቁርባን ነው። ጥምቀቱ መደረግ ያለበት በተፈጥሮ ኗሪ ውኃ ለምሳሌ እንደ ወንዝ፣ ባሕር ወይም ምንጭ ውስጥ እንዲሆን ያስፈልጋል።

ከዚህ ቀድሞ የውኃ ጥምቀትመንፈስ ቅዱስ የተቀበለው መጥምቅ በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ያጠምቀዋል። ተጠቃሚውም ራሱን አጎንብሶ ወደ ታች ሲመለከት በውኃ በሙሉ እንዲታጠብ ነው።»

[ለማስተካከል] እግር ማጠብ

«የግሮች ማጠብ ምስጢር ሰው ከጌታ ኢየሱስ ጋር ድርሻ እንዲኖረው ያስችለዋል። ደግሞ ፍቅር፣ ቅድስና፣ ትሕትና፣ ይቅርታ እና አገልግሎት እንደሚያስፈልጉት እንደ ዘወትር ማስታሰቢያ ያገለግላል።

የውኃ ጥምቀት የተቀበለ ሰው ሁሉ እግሮቹን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንዲታጠብ አለበት። በሚገባበት ጊዜ እርስ በርስ መታጣጠብ ሊሠራ ይችላል።»

[ለማስተካከል] ቅዱስ ቁርባን

«ቅዱስ ቁርባን የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ መሞት የሚያከብረው ምስጢር ነው።

ዘላለማዊ ሕይወት እናገኝ ዘንድ በመጨረሻም ቀኝ እንነሣ ዘንድ፣ ከጌታችን ሥጋ ወደም ለማሳተፍ ከሱም ጋር ለመቈረብ ያስችለናል። ይኸው ቁርባን እስከሚቻል ድረስ ብዙ ጊዜ ይደረጋል። አንድ ቂጣ እና የወይን ጭማቂ ብቻ ይጠቀማል።»

[ለማስተካከል] የሰንበት ቀን

«የሰንበት ቀን፥ የሣምንቱ ሰባተኛ ቀን (ቅዳሜ) በእግዚአብሔር የተባረከና የተቀደሠ ቅዱስ ቀን ነው። የእግዚአብሄርን ፍጥረትና መድኃኒት ለማስታወስና በሚመጣው ሕይወት የዘላለማዊ ዕረፍት ተስፋ ከማድረግ ጋራ በጌታ ጸጋ መሠረት ይከብራል።»

[ለማስተካከል] ተጨማሪ ትምህርቶች

በኋላ በ1980ዎቹ የዕውነተኛ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን 10 መሠረታዊ እምነቶች ለመሆን በነዚህ 5 ዋና ትምህርቶች ላይ ሌሎች ተጨመሩ፦

[ለማስተካከል] ኢየሱስ

ኢየሱስ ክርስቶስ ቃል ሥጋ ሆኖ በመስቀል ላይ ስለ ኃጢአተኞች ቤዛነት የሞተው፣ በሦስተኛው ቀን ከሙታን የተነሣውና ወደ ሰማያት ያረገው ነው፤ እርሱ የሰው ልጆች ብቸኛ አዳኝና የሰማይና የምድር ፈጣሪ እንዲሁም እውነተኛ አምላክ ነው።

«እየሱስ ክርስቶስ፣ ስጋ የሆነው ቃል፣ ሀጥያተኞችን ለማዳን በመስቀሉ ላይ ሞተ፣ በሶስተኛው ቀንም ተነሳ እና ወደ ሰማይ አረገ። የሰው ልጅ አዳኝ፣ የዚች ዓለምና የሰማይ ፈጣሪ፣ አንዱና ብቸኛው አምላክ እሱ ብቻ ነው።».

[ለማስተካከል] መጽሐፍ ቅዱስ

«መጽሀፍ ቅዱስ፣ አዲሱና ያለፈውን ኪዳን ይዞ፣ በእግዚአብሄር ነው የተናሳሳው፣ ብቸኛው የተጻፈ እውነት ነው፣ የክሪስቲያን አኗኗር ደንብ ነው።».


[ለማስተካከል] ደኀንነት

«ደኀንነት በእግዚአብሔር ጸጋ በእምነት ይሰጣል። ቅድስናን ለመከተል፣ እግዚአብሔርን ለማክበርና ሰዎችን ለመውደድ፤ አማኞች በመንፈስ ቅዱስ ላይ መታመን አለባቸው።»

[ለማስተካከል] እውነተኛ ቤተክርስቲያን

«በ'ኋለኛ ዝናብ' ግዜ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የተመሠረተው እውነተኛ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን የሃዋርያዊ ዘመን የታደሰ እውነተኛ ቤተ ክርስቲያን ነው።»

[ለማስተካከል] ዳግመኛ ምጣት

«የጌታው ዳግመኛ ምጽአት የሚደርሰው ዓለምን እንዲፈርድ ከሰማይ በወረደበት በመጨረሻ ቀን ነው። በዚያን ግዜ ጻድቃን የዘላለምን ሕይወት ይቀበላሉ፤ ክፉዎችም ለዘላለም ይኮነናሉ።»

የኔ መሣርያዎች

Variants
Actions
የማውጫ ቁልፎች
ጠቃሚ መሣሪያዎች
በሌሎች ቋንቋዎች