ኢየሱስ
ከWikipedia
ኢየሱስ (ዕብራይስጥ: ישוע ፣ የሹዓ) የክርስትና ሃይማኖት መሰረት ነው። ክርስቶስ ማለት በግሪክ ቋንቋ Χριστός ነው፤ ይህም መሢሕ (ከዕብራይስጥ ማሺያሕ ወይም 'የተቀባ') ማለት ነው። እየሱሰ በብዙ አብያተ ክርስትያናት፤ አምላክ እና ፈጣሪ ነው ተብሎ ይታመናል። እንዲሁም አንዳንድ ሃይማኖቶች የእግዚአብሔር መልዕክተኛ ነው ሲሉ አንዳንዶቹ ደግሞ ነቢይ ነው ብለው ያምናሉ።
[ለማስተካከል] የኢየሱስ ጥቅሶችና ትምህርቶች
አብያተ ክርስቲያን ቅዱስ ብለው የሚቆጠሩት 4 መጻሕፍት ወንጌሎች የኢየሱስን ሕይወት ታሪክ ይገልጻሉ።
በነዚህ ወንጌሎች መሠረት ኢየሱስ ሲያስተምር ብዙ ጥቅሶች ይገኛሉ። ለምሳሌ፦
- «የአሕዛብ አለቆች እንዲገዙአቸው ታላላቆቹም በላያቸው እንዲሠለጥኑ ታውቃላችሁ። በእናንተስ እንዲህ አይደለም...» (ማቴ 20፡25)
በዚሁ ጥቅስ ኢየሱስ ዓለሙን እንደ ገለበጠ ተብሏል። በዚያን ግዜ ይሁዳ በባዕድ አረመኔ ሕዝብ ከባድ ገዥነት ሥር ነበረችና፣ የአይሁዶች ሊቃውንት ከትንቢት የተነሣ ከሮሜ ዕጅ የሚያድናቸውን መሢሕ ይጠብቁ ነበር። ይህ አይነት ትንቢት ቢገኝም ኢየሱስ ያንግዜ በጦርነት ስላላነሣ የአይሁድ መሪዎች ሊቀበሉት ፈቃደኛ አልነበሩም።
ደግሞ «እግዚአብሔር ምኑን ይፈልጋል?» ለሚለው ለዘመናት ፍልስፍና ጥያቄ በመመልስ ኢየሱስ በብሉይ ኪዳን ትንቢተ ኢሳይያስ ውስጥ ይህን መልስ አገኝቶ ብዙ ግዜ ያጠቁመው ነበር፦
- «ምሕረት እፈልጋለሁ እንጂ መሥዋዕት አይደለም።»
ለሚሰሙት ተከታዮቹ ግን አዲስ ጥያቄ ጠየቃቸው፣ እንዲህ ሲል፦
- «ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?» (ማርቆስ 8:36)
በወንጌላት በኩል እጅግ በርካታ ተመሳሳይ ትምህርቶች በቀላሉ ሊነቡ ይቻላል።
[ለማስተካከል] ተጨማሪ ማጣቀሻዎች:-
- ስለ ኢየሱስ የበለጠ ለማወቅ "ኢየሱስ ዶት ኮም" የተባለ ድረገጽን ይጎብኙ።
- መጽሓፍ ቅዱስ