ኢየሱስ

ከውክፔዲያ
የናዝሬቱ ኢየሱስ ክርስቶስ
እየሱስ ክርስቶስ የመንግሥተ ሰማይ መግቢያ በር።
እየሱስ ክርስቶስ የመንግሥተ ሰማይ መግቢያ በር።
ነዋ በግዑ ለእግዚብሔር ዘይሐትት ወያሰስል ኃጢያተ ዓለም
የተወለደው በ፩ኛው ዓ.ም. በቤተልሔም
ዓመተ ምሕረትም ስለሱ ተቆጠረ
የእናት ስም ማርያም
የአባት ስም እግዚአብሔር አብ (ያሳደገው ቅዱስ ዮሴፍ እንደ አባት)
በሰማይ መንፈሳዊ እናት በምድር ሥጋዊ አባት የለውም
ዓመታዊ ዋና በዐላት ፱ሲሆኑ ዋና ዋናዎቹ
ገና (ልደት)
ጥምቀት
ስቅለት
ትንሳዔ (ፋሲካ)
ያደገበት ቦታ ናዝሬት-ገሊላ
ያረፈው በ፴፫ኛው ዓ.ም. በእየሩሳሌም
ከሙታን ተለይቶ የተነሳው ባረፈ በ፫ኛው ቀን በእየሩሳሌም
የሚመለከው በመላው የክርስትና ሃይማኖት እምነት ተከታይ ሕዝብ [1]
ስለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መሰቀል ። አድናቆት ለkiduel channel


በ14ኛው ከፍለ ዘመን መሰራቱ የሚታመን የኢየሱስና የማሪያም ምስል ፣ በተጨማሪ ይህ ስዕል እቴጌ ምንትዋብማርያምና ለልጇ እየሱስ ክርስቶስ ስትሰግድ ለራሷ ማስታወሻ ያሣለችው ስዕል ነው።

ኢየሱስ (በዕብራይስጥ: ሲጻፍ ישוע ፣ ሲነበብ፡ የሹዓ፣ ትርጉሙም፡ የሚያድን ማለት ነው) የክርስትና ሃይማኖት መሰረት ነው። ክርስቶስ ማለት (በግሪክ ቋንቋ ሲጻፍ Χριστός ፤ ይህም መሢሕ ማለት ነው)፤ (በዕብራይስጥ ማሺያሕ ወይም 'የተቀባ' ማለት ሲሆን በተጨማሪም ዐማኑኤል ይባላል ትርጉሙም እግዚአብሔር ከኛ ጋር ሆነ) ማለት ነው ። ከሥላሴ አንዱ አካል ወልድ ኢየሱስ ነው።


ኢየሱሰ በክርስትና ሃይማኖት አንድ አምላክ ከሚሆኑት አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ማለትም ከሥላሴ አንዱ ወልድ እሱ ነው ፤ ይህም ወልድ ፣ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ

የኢየሱስ ክርስቶስ ልደትና ጥምቀት

እንደ ሰው በምድር ተመላልሶ የአባቱን መንግሥት አስተምሮ ለሰው ልጅ መዳን ሲል ራሱን አሳልፎ የሰጠ በመጨረሻም ከሞት ተነስቶ መንፈስ ቅዱስ እንዲተካው አድርጎ ወደ ሰማይ አርጎ በአባቱ ቀኝ የተቀመጠ ይህን ዓለም ለመፍረድ ዳግም ምፃቱ የሚጠበቅ አምላክ እና ፈጣሪ ነው ። ስለኢየሱስ የበለጠ ለመረዳት አዲስ ኪዳንን በተለይ ወንጌል በአራቱ ሐዋርያት ፣ በቅዱስ ማርቆስቅዱስ ሉቃስቅዱስ ዮሐንስቅዱስ ማቴዎስ የተፃፈውን ያንብቡ ።
ከድረ ገጾቹ አንዱን ለመመልከት እዚህ ላይ ይጫኑ

ክርስቶስ በኣሕያ ውርንጫ ላይ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ


እንዲሁም አንዳንድ ሃይማኖቶች ደግሞ የእግዚአብሔር መልዕክተኛ ነው ሲሉ አንዳንዶቹ ደግሞ ነቢይ ነው ብለው ያምናሉ።

ስምና ልደትተጨማሪ ማስረጃ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

«ኢየሱስ» የሚለው ስም ፦ በግሪክኛ «ኤሱስ» Ἰησοῦ በቀዳማይ እብራይስጥ «ያህሹአ» יְהוֹשֻׁעַ ፣ በደሃራይ እብራይስጥ «ያሱአ» יֵשׁוּעַ ፣ በአረማይክ «ዔሳዩ» ܝܫܘܥ ፤ በቀዳማይ አረብኛ «ዒሳ» عيسى ፤ በደሃራይ አረቢኛ «የሱዐ» يسوع ሲሆን ትርጉሙ ከእብራይስጥ «ያህዌ መድሃኒት ነው» ማለት መድኃኒያለም የሚል ፍቺ አለው፤ በተለይ ኢየሱስ ሰዎች ሲጠሩበት የነበረ የሰው ስም መሆኑን ለማሳየት ለሌሎች ሰዎች አገልግሎት ላይ ውሏል።

ማርያም ልጅ ኢየሱስ ከሌሎች ኢየሱሶች ለመለየት ባደገበት አገር ስም በናዝሬት የናዝሬቱ ኢየሱስ ይባላል፦ ሉቃስ 18፥37።

ከዚህም በቀር «ኢያሱ» (ወይም በግዕዝ «ኢየሱስ»፣ በግሪክ «ኢዬሶውስ»፣ በዕብራይስጥም «ያህሹዓ») የተባሉት ሌሎች ግለሠቦች ከብሉይ ኪዳን እና ከአዲስ ኪዳን ማየት ይቻላል፦

እንደ ክርስትና እምነትና ወንጌሎች ኢየሱስ ከድንግል ማርያም እና ከመንፈስ ቅዱስቤተ ልሔምይሁዳ ተወለደ። ሳዱላዋ ማርያምና እጮኛዋ ዮሴፍ ለሕዝብ ቁጠራ በይሁዳ ስለ ተገኙ የቤት መጻተኞች ሆነው በጋጣ ተኝተው ነበር፤ ኢየሱስም በግርግም የተኛ እንጂ አልጋ አልነበረም። ገሊላ ግን በስሜን እስራኤል ወይም ሰማርያ ቤተሠቡ የተገኙበት ኢየሱስም የታደገበት ሀገር ነበረ።

የኢየሱስ ጥቅሶችና ትምህርቶች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ኢየሱስ በመቃብሩ ተብሎ የሚታመነው የቶሪኖ ከፈን ፎቶ ኔጋቲቭ

ቤተክርስቲያን ቅዱስ ብላ የምትጠቀምባቸው ፬ መጻሕፍት ወንጌሎች ማቴዎስማርቆስሉቃስዮሐንስ እንደተጻፉት የኢየሱስን ትምህርትና ከሞላ ጐደል የሕይወት ታሪኩን ይገልጻሉ።

በነዚህ ወንጌሎች መሠረት ኢየሱስ ሲያስተምር ብዙ ጥቅሶች ይገኛሉ። ለምሳሌ፦

«የአሕዛብ አለቆች እንዲገዙአቸው፡ ታላላቆቹም በላያቸው እንዲሠለጥኑ ታውቃላችሁ። በእናንተስ እንዲህ አይደለም...» (ማቴ 20፡25)

በዚሁ ጥቅስ ኢየሱስ ዓለሙን እንደ ገለበጠ ተብሏል። በዚያን ጊዜ ይሁዳ በባዕድ አረመኔ ሕዝብ ከባድ ገዥነት ሥር ነበረችና፣ የአይሁዶች ሊቃውንት ከትንቢት የተነሣ ከሮሜ ዕጅ የሚያድናቸውን መሢሕ ይጠብቁ ነበር። ይህ አይነት ትንቢት ቢገኝም ኢየሱስ ያንጊዜ በጦርነት ስላላነሣ የአይሁድ መሪዎች ሊቀበሉት ፈቃደኛ አልነበሩም።

ደግሞ «እግዚአብሔር ምኑን ይፈልጋል?» ለሚለው ለዘመናት ፍልስፍና ጥያቄ በመመልስ ኢየሱስ በብሉይ ኪዳን ትንቢተ ኢሳይያስ ውስጥ ይህን መልስ አገኝቶ ብዙ ጊዜ ያጠቁመው ነበር፦

«ምሕረት እፈልጋለሁ እንጂ መሥዋዕት አይደለም።»

ለሚሰሙት ተከታዮቹ ግን አዲስ ጥያቄ ጠየቃቸው፣ እንዲህ ሲል፦

«ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?» (ማርቆስ 8:36)

በወንጌላት በኩል እጅግ በርካታ ተመሳሳይ ትምህርቶች በቀላሉ ሊነቡ ይቻላል።

ደግሞ ይዩ፦

ኢየሱስ ማን ነውባጭሩ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ኢየሱስ ለኦስሮኤና ንጉሥ ለ5ኛው አብጋር የላከው ተብሎ የሚታመነው ግርማዊው የጄኖቫ ቅዱስ መልክ

ተዋሕዶ አብያተ ክርስትያናት እምነት ትምህርት፣ የኢየሱስ ሰብአዊና መለኰታዊ ባሕርይ አንድ (ተዋሕዶ) ነው። ከካልኬዶን ጉባኤ ጀምሮ ግን በሮማ ቤተክርስትያን ትምህርት ዘንድ በሁለት ልዩ ልዩ ሰብአዊና መለኰታዊ ባሕርዮች ተለይቷል። ኢየሱስ ወልድ ሆኖ ከሥላሴ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ) አንዱ ክፍል በመሆኑ አምላክ ነው በማለት በንቅያ ጸሎተ ሃይማኖት ይስማማሉ። «ቃሉ ሥጋ ሆነ» ሲባል፣ ፈጣሪው ወደ ፍጥረቱ በሙሉ በመግባት ዓለሙን ለማዳን ኃይልና ፈቃድ እንዳለው ገለጸ ለማለት ነው።

ከዚህ በላይ ስለ ኢየሱስ ማንነት ብዙዎች አብያተ ክርስትያናት ከአዲስ ኪዳን ጠቅሰው እንደሚያስተምሩት የሚከተለውን እንረዳለን

1. ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ከሁለት ሺህ ዓመት በፊት በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ አንድ እንግዳ ሰው ብቅ አለ፡፡ ይህ ሰው በአለም ውስጥ የተወለደ ቢሆንም፣ ልክ እንደማንኛውም ሰው ሰብአዊ ማንነት ቢኖረውም ተራ ሰው አልነበረም። ከድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ ተፀንሶ ወደ ምድር የመጣው፣ በሰው አምሳል የተገለጠው ራሱ እግዚአብሔር ነው፡፡ ይህ ሰው (የእግዚአብሔር ልጅ) ነው (ሉቃስ 1፡26-35)፣ (ዮሐንስ 1፡1 እና ዮሐንስ 1፡14)።

በብሉይ ኪዳን ስለሚመጣው መሢህ (ክርስቶስ) ሲተነበይ ከመጠሪያዎቹ አንዱ አማኑኤል በዕብራይስጥ «ኢሜኑ» (ከኛ ጋር) «ኤል» (አምላክ) ወይም አምላክ ከኛ ጋራ ማለት ነው። ምድር የእግዚአብሔር መረገጫ እንደ ተባለች (ኢሳይያስ 66:1 እና ማቴ. 5:35) ወደፊት «ከወንዝ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ» ለዘላለም የሚነግስ ብለው የተነበዩለት አምላክ የሚሉት እግዚአብሔር ነው።

2. ኢየሱስ ወደ ምድር የመጣው ለተለየ ተልእኮ ነው[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  • የሰው ልጅ ከጠፋበት መንገድ ሊመልስ (ሉቃስ 19፡10)።
  • ከጨለማ ስልጣን ሊያድነን (ቆላሲያስ 1፡13)፡፡
  • ነፍሱን ለእኛ ቤዛ አድርጎ ሊሰጥ፤ ደሙን ከፍሎ ሊገዛን (ማቴ 20፡28)፡፡

* በሕይወታችን ያለውን የሰይጣንን ሥራ ሊያፈርስ (1ዮሐ 3፡8)፡፡

  • የዘላለም ሕይወት ሊሰጠን (1ዮሐ 5፡11፣12)፡፡ በተጨማሪ ዮሐንስ 3፡16፣17 እና ዮሐንስ 10፡10 ይመልከቱ፡፡
  • አዲስ ልደት በመስጠት የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ሊያደርገን (ዮሐ 1፡12)፡፡ በተጨማሪ 1ዮሐ 3፡1.2 ይመልከቱ
  • ከአብ ጋር የነበረንን ሕብረት ለማደስ (1ዮሐ 1፡3)።

3. ኢየሱስ እግዚአብሔር ምን እንደሚመስል ሊያሳየን መጣ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

(ዮሐ 14፡7-11)፡፡ በተጨማሪ ዮሐንስ 1፡18 ይመልከቱ።

  • የእግዚአብሔርን ፍቅር አሳየን (1ዮሐ 4፡9፣10)፡፡ በተጨማሪ ሮሜ 5፡8 ይመልከቱ።
  • የእግዚአብሔርን ኃይል አሳየን፣ የታመሙትን፣ ሽባዎችን እና አይነስውራንን ፈወሰ (ማቴ 4፡24)፡፡ በተጨማሪ ዮሐንስ 9፡1-7 ይመልከቱ።
  • ርኩሳን መናፍስትን አስወጣ (ማር 1፡34)፡፡ በተጨማሪ ማርቆስ 5፡1-17 ይመልከቱ።
  • ተአምራትን አደረገ (ማር 4፡37-41)፡፡ በተጨማሪ ዮሐንስ 6፡1-21 ይመልከቱ።
  • ሙታንን አስነሳ (ዮሐ 11፡43፣44)፡፡

4. ኢየሱስ መከራችንን ተቀበለ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ኢየሱስ በምድር ሕይወቱ እኛ የምንቀበለውን የሕይወት ችግሮች በሞላ አይቷል፤ ስለዚህም ሊራራልን ይችላል። (ዕብ 4፡15)፡፡ በተጨማሪ ማቴዎስ 8፡17 ይመልከቱ።

5. ኢየሱስ ስለእኛ በመስቀል ላይ ሞተ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ኃጢአተኛ ሰዎች በሀሰት ኢየሱስን እንደ ወንጀለኛ ከእንጨት በተሰራ መስቀል ላይ ቸነከሩት፡፡ ራሱን ከዚህ ማዳን ቢችልም፣ አላደረገውም፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር አለሙን የሚያድነው በእርሱ የመስቀል ላይ ሞት ነበርና፡፡ ስዚህ ኢየሱስ ስለ እኛ ሞተ! (ማር 15፡16-39 ያንብቡ) (1ጴጥ 2፡24)፡፡ በተጨማሪ ኢሳያስ 53፡5፣6 ያንብቡ፡፡

6. ኢየሱስ ስለእኛ ከሙታን መካከል ተነሳ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ከሦስት ቀን የመቃብር ቆይታ በኋላ እግዚአብሔር ልጁን ከሙታን መካከል አስነሳው! (ማቴዎስ 28 ያንብቡ)፡፡ ትንሳኤውም ጭምር ለእኛ ሲል ነበር፡፡ (ኤፌ 2፡4-6)፡፡ በተጨማሪ ሮሜ 6፡4 ያንብቡ፡፡ አንድእግዚሀቢዬርበሚሄንበአቦበወልድ

7. ኢየሱስ ለእኛ የሰማይን ደጅ ከፈተልን[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በምድር ላይ የነበረውን ሥራ በፈፀመ ጊዜ ኢየሱስ ወደአባቱ ዘንድ ወደሰማይ አረገ፡፡ ይህም ጭምር ለእኛ ነበር፡፡ ምክንያቱም አሁንና ለዘላለሙ ከእርሱ ጋር አብረን ለመኖር ወደ እግዚአብሔር መገኛ የምንሄድበት መንገድ ከፍቶልናል፡፡ (ዕብ 10፡19-22)፡፡ በተጨማሪ ዮሐንስ 14፡1-3 ይመልከቱ። ለተጨማሪ መረጃ የሚከተለውን አድራሻ ይጎብኙ፡ http://bible-question-and-answer.blogspot.com/2012/02/blog-post.html

ተጨማሪ ማጣቀሻዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ በፕዪው የጥናት መዐከል መሠረት : በ፳፻፲፭ ዓ.ም. በተደረገው ግምት የዓለም ክርስቲያን ሕዝብ በ፳፻፶ ዓ.ም. ወደ ፫ቢሊዮን ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል