ማርያም

ከውክፔዲያ
ቅድስት ድንግል ማርያም
ንግሥተ ሰማይ ወምድር
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ምስለ ፍቅርን አቅፋ
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ምስለ ፍቅርን አቅፋ
እርግበ መንግሥተ ሰማያት።
የተወለደችው 15 ዓመት ከክርስቶስ ልደት በፊት
የትውልድ ሀገር እስራኤል፣ ይሁዳ ክፍለሀገር፣ በገሊላ አውራጃ፣ ናዝሬት በምትባል ስፍራ (አሁን ሊባኖስ ውስጥ ይገኛል)
የምትከበረው በየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን
ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያኖችና
በአንዳንድ
ክርስቲያን ዲኖሚኔሽን (አንግሊካን፥ የጥንት ሉተ...)
የእናት ስም ሐና
የአባት ስም እያቄም
አንድዬ ልጅዋ ኢየሱስ ክርስቶስ
በዓላት ፴፫ ሲሆኑ በየወሩ በ፳፩ ቀንና በተጨማሪ ዋና ዋናዎቹ፣
- የተወለደችበት ቀን ልደታ ግንቦት ፩
- ለአይሁድ ቤተ መቅደስ የተሰጠችበት ባአታ ማርያም ታኅሣሥ ፫
- ስደቷን ጨርሳ ወደ ትውልድ ሀገሯ የገባችበት ቁስቋም ማርያም ኅዳር ፮
- ቃል ኪዳን የተቀበለችበት ኪዳነ ምረት የካቲት ፲፮
- በጎሎጎታ እየተመላለሰች የጸለየችበት ሰኔ ጎሎጎታ ሰኔ ፳፩
- ያረፈችበት ወይም የሞተችበት ቀን ጥር ፳፩ አስትሮ ማርያም በ፷፬ ዓመቷ
- ዕርገቷና ትንሣኤዋ ፍልሠታ ነሐሴ ፲፮
ውል ውል አለኝ ደጅሽ አድናቆት ለአኪልዳማ channel


ማርያም ምስለ ፍቁርን ይዛ አክሱም ፅዮንማርያም የሚገኝ ስዕል


ድንግል ማርያምክርስትናና፣ በእስልምና እምነቶች መሠረት የከበረችው የኢየሱስ ክርስቶስ እናት ነች። በክርስትና እምነት የኢየሱስ ክርስቶስ እናት ማለትም የወልድ እናት ድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ ግብር ኃይል ሥላሴ ምርጫ በድንግልና ፀንሳ በድንግልና እንደ ወለደችው ይታመናል ። በእግዚአብሔር ህሊና ከፍጥረት በፊት እንደነበረች ኦዘ-ም፡፫ ቁ፡፲፭ ያስረዳል[1] የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ማርያምን በጣም ከመወደዷ የተነሳ ከ፻ በላይ በሰየመቻት ስሞቿ ትጠራታለች (የቅድስት ድንግል ማርያም ስሞች)::

አንዱ የእመቤታችን ቅድስ ድንግል ማርያም አስደናቂ አባባል ደሞ "ትውልድ ሁሉ ብፅእት ይሉኛል" ሉቃ.ም፣፩ ቁ.፵፯ ፶፭ ብላ ከ፪ሺ ዓመት በፊት የጸለየቸው ወይም የተናገረቻችው ቃላቶች ናቸው ።

ሙስሊሞች ደግሞ መሪማ የኢየሱስ (ኢሳ) እናት ይልዋታል።

በአለም ላይ ፫ ታላላቅ እምነቶች[2] ዘንድ እስዋም ልጅዋም ትልቅ ክብርና ቅድስና በተለይ ለልጇ መመለክ ገንዘባቸው ነው።

Podcasts ለማዳመጥ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ውዳሴ ማርያም እንድምታ podcast

ቅዳሴ ማርያም እንድምታ podcast

ከድረገጾችዎ አንዱን ለማየት እዚህላይ ይጫኑ
ወይም ይህን ይጫኑ

ክርስትና[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በክርስትና እምነት ድንግል ማርያም ሰው ሁኖ የመጣዉ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ እናት ነች። ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ ከእግዚአብሔር አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንዱ ተወላዲ ማለትም (ወልድ) ሲሆን ፣ ወላዲ ደግሞ (አብ) ነው ፣ ቀጥሎም ሰራጺ (መንፈስ ቅዱስ) ይሆናል ፤ በተጨማሪ ወልድ ጌታ ወይም ክርስቶስመሢሕ ይባላል። እናቱ ማርያም እግዚአብሔር የተባለውን ወልድ ለመውለድ ስለ ተመረጠች እና ብቁ ሆና ስለተገኘች ከሴቶች ሁሉ ይልቅ ብጹዕት ፣ ቅድስት ፣ በግሪክ ቴዎቶከስ ማለትም የእግዚአብሔር እናት ትባላለች።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከ 34 ዓ.ም ጀምራ ክርስትናን በኢትዮጵያ ምድር የሰበከች ጥንታዊት ቤተክርስቲያን ሥትሆን ምድቧም ከ ኦርዮንታል አብያተ ክርስቲያናት ነው:: እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሥላሴ አካላት አንዱ ወልድ፣ አምላክ ነው::ይህ አምላክም ወይም እግዚአብሔር ወልድ ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ተወለደ::በሌላ አገላለጽ አምላክ ሰው ሆነ::በዚህም ምክንያት ቅድስት ድንግል ማርያምን የጌታ እናት ወይም የእግዚአብሔር እናት(ወላዲተ አምላክ) ትባላለች:: ቤተክርስቲያኗ ልጇን ኢየሱስ ክርስቶስንም አምላክ ፣ ወልደ አምላክ ፣ ወልደ ማርያም ፣ ወልድ፣ ቃል ብላ ትጠራዋለች:: ድንግል ማርያምን ደግሞ እመቤት ፣ ቅድስተ ቅዱሳን ፣ እግዝእትነ ማርያም ፣ የጌታ እናት ፣ ወላዲተ አምላክ ፣ ቅድስት፣እመ ብርሃን ፣ እመ አምላክ፣ንጽሕተ ንጹሃን ቅድስተ ቅዱሳን፣ጽዮን ወዘተ በማለት ትጠራታለች::ቅድስት ድንግል ማርያምን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከአዳም በደል ወይም ከጥንተ አብሶ ነጻ ሆና በአዳም ባህርይ እንደ እንቁ ስታበራ የኖረች አደፍ ጉድፍ የሌለባት ፣ ከመርገመ ሥጋ ከመርገመ ነፍስ የነጻች ፣ እንደሆነች ታምናለች። በሌላው ወገን ጥንተ አብሶ ነበራት ለዚህም ማስረጅያ "ጸሎተ እግዝእትነ ማርያም" ተብሎ የሚጠራው በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 1 ቁጥር 47 እግዚአብሔርን "መድኃኒቴ" ብላ ማመስገነዋ ነው የሚሉም አሉ ። ሁለቱም ወገን ግን እግዚአብሔር ወልድ ሥጋዋን ከተዋሃደ በፊት እንዳነጻት ማደሪያው እንድትሆን እንዳስጌጣት ከወለድችሁም በኋላ በድንግልኗና በንፅህኗ እንደኖረች፣ ለዘለዓለም በዚሁ ሁኔታ ጸንታ እንደምትኖር ያምናሉ። ከፍጡራን በላይ ከፈጣሪ በታች የሆነች፣ የሰማይ የምድር ንግስት ፣ እንደሆነች ቤተክርስቲያን ታስተምራለችና ። አንዱ የእመቤታችን ቅድስ ድንግል ማርያም አስደናቂ አባባል ደሞ "ትውልድ ሁሉ ብፅእት ይሉኛል" ሉቃ.ም፣፩ ቁ.፵፯ ፶፭ ብላ ከ፪ሺ ዓመት በፊት የጸለየቸው ወይም የተናገረቻችው ቃላቶች ናቸው ። ይህም መንፈስ ቅዱስ የሞላባት ወልድ የተዋሀዳት አብ የመረጣት ፍፁምነት የተገለፀባት ከሰው ሁሉ ተለይታ መከበር የሚገባት መሆኑዋን አረጋግጦ ያስረዳል ።

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቃል ኪዳኑን ስትቀበል

ጸሎተ ማርያም ሉቃስ ም፩ ፣ ፵፯ - ፶፭

ነፍሴ፡ጌታን፡ታከብረዋለች፥መንፈሴም፡በአምላኬ፡በመድኀኒቴ፡ሐሴት፡ታደርጋለች፤ የባሪያዪቱን፡ውርደት፡ተመልክቷልና።እንሆም፥ከዛሬ፡ዠምሮ፡ትውልድ፡ዅሉ፦ብፅዕት፡ ይሉኛል፤ ብርቱ፡የኾነ፡ርሱ፡በእኔ፡ታላቅ፡ሥራ፡አድርጓልና፤ስሙም፡ቅዱስ፡ነው። ምሕረቱም፡ለሚፈሩት፡እስከ፡ትውልድና፡ትውልድ፡ይኖራል። በክንዱ፡ኀይል፡አድርጓል፤ትዕቢተኛዎችን፡በልባቸው፡ዐሳብ፡በትኗል፤ ገዢዎችን፡ከዙፋናቸው፡አዋርዷል፤ትሑታንንም፡ከፍ፡አድርጓል፤ የተራቡትን፡በበጎ፡ነገር፡አጥግቧል፤ባለጠጋዎችንም፡ባዷቸውን፡ሰዷቸዋል። ለአባቶቻችን፡እንደ፡ተናገረ፥ለአብርሃምና፡ለዘሩ፡ለዘለዓለም፡ምሕረቱ፡ትዝ፡እያለው፡

እስራኤልን፡ብላቴናውን፡ረድቷል።

የቅድስት ድንግል ማርያም ትውልድ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ቅድስት ድንግል ማርያም አባቷ ኢያቄም እናቷ ደግሞ ሃና ይባላሉ::የተፀነሰቸው በእለተ እሁድ ነሐሴ ፯ ቀን ሲሆን የተወለደቸውም ግንቦት ፩ ነው::እመቤታችን እግዝትእነ ማርያም የተወለደችበት እለት በአባት እናቷ ቤት ፍስሃ ደስታ ተደረገበት ፤ ቤቱንም ብርሃን መላው ፤ በ፰ኛውም ቀን ማርያም ብለው አወጡላት::ስለምን ማርያም ብለው አወጡላት ቢሉ:እነሆ በዚህ አለም ከሚመገቡት ሁሉ ምግብ ለአፍ የሚጥም ለልብ የሚመጥን ማር ነው:በገነትም በህይወት የተዘጋጁ ጻድቃን ቅዱሳን ያም የሚባል ምግብ አላቸው ::ከዚ ሁሉ የበለጥሽ የከበርሽ ነሽ ሲሉ ስለዚህ ማርያም ብለው አወጡላት:: እመቤታችን ማርያም ለእናት ለአባቷ አንዲት ስትሆን የተወለደቸው በጸሎት በመሆኑና የስለት ልጅ በመሆኗ እናትና አባቷ ለእግዚአብሔር በተሳሉት መሰረት ፫ ዓመት ሲሞላት ወደ ቤተመቅደስ ወሰደው ለካህኑ ለዘካርያስ አስረከቧት::እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በተወለደች በሦስት ዓመቷ እናቷ ሐና አባቷ ኢያቄምን፡- “ይህች ብላቴና ሆዷ ዘመድ ሳይወድ፣ አፏ እህል ሳይለምድ “ለእግዚአብሔር በገባነው ቃል መሠረት ወስደን ለቤተ መቅደስ አንሰጣትምን?” ‘የሰጠ ቢነሣ የለበት ወቀሳ’ እንዲሉ አንዳች ነገር ብትሆንብን ከልጃችንም ከእግዚአብሔርም ሳንሆን እንዳንቀር” አለችው፡፡ እርሱም፡- “ፍቅርሽ ይለቅልሽ ብዬ ነው እንጂ እኔማ ፈቃዴ አይደለምን?” አላት፡፡ወላጆቿ ይህን ተነጋግረው እንዳበቁ ሕጻን ልጃቸውን ማርያምን ወስደው ለቤተ መቅደስ ሰጧት፡፡ በዚያን ጊዜ የነበረው ሊቀ ካህናት ዘካርያስ ይባላል፤ እርሱም ስለ ምግቧ ነገር ሊያስወስን መጥቅዕ (ደወል) ደውሎ ሕዝቡን ሰብስቦ እየተወያዩ ሳለ የእግዚአብሔር መልአክ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ፋኑኤል የሰማይ ኅብስትና የሰማይ ጽዋ ይዞ ከሰማይ ወርዶና ረብቦ ታየ፡፡ብላቴናይቱንም መልአኩ ፈጥኖ ወርዶ አንድ ክንፉን አንጥፎ አንድ ክንፉን ደግሞ ጋርዶ በሰው ቁመት ያህል ከምድር አስለቅቆ ከፍ አድርጓትና መግቧት ዐረገ፡፡ ከዚህ በኋላ ካህናቱና ሕዝቡ “የምግቧ ነገር ከተያዘልንማ ከሰው ጋር ምን ያጋፋታል” ብለው ሕጻን ማርያምን ከወላጆቿ ተቀብለው ወደ ቤተ መቅደስ አግብተዋት በዚያ ፲፪ ዓመት ኖራለች፡፡ይህም ሲደመር ጠቅላላ ፲፭ ዓመት ሆናት ማለት ነው::በዚህ ስዓት አይሁድ ከበተመቅደስ ትውጣልን ብለው አመለከቱ ፤ ለጻድቁ ለቅዱስ ዮሴፍም እንዲጠብቃት ታጨች ፤ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል አበሰራት::በ ፲፭ አመቷ እግዚአብሔር ወልድን ፀነሰች::

የቅድስት ድንግል ማርያም ስሞች:- የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን «እስመ ስሙ ይመርህ ኀበ ግብሩ» በማለት ስም ግብርን ሁኔታን ማንነትን ይገልጻል ይላሉ፡፡በዚህም መሰረት ቤተክርስቲያኗ ለስመ ድንግል ማርያም ዘርፍ /ቅጽል/ አልያም ምትክ አድርጋ የምትጠቀምባቸው ምሥጢራዊና ረቂቅ ትርጉም ያላቸው ንጽሕናዋን፣ ቅድስናዋን፣ ድንግልናዋን፣ ብፅእናዋን ወዘተ የሚመሰክሩ በርካታ ስሞች ሰይማላታለች፡፡ከነዚህም መካከል ከብዙ በጥቂቱ:ምልዕተ ጸጋ ፣ እምነ /«ም» ጠብቆ ይነበብ/ ጽዮን ፣እመ ብርሃን ሰአሊተ ምሕረት ፣እመቤታችን ፣ቤዛዊተ ዓለም፣ ወላዲተ አምላክ ፣ኪዳነ ምሕረት ወዘተ..

ቅድስት ድንግል ማርያም በ 64 ዓመቷ ካረፈች በኋላ እንደ ልጇ በሦስተኛው ቀን ማረጓን ቤተክርስቲያኑ ታስተምራለች::

ቅድስት ድንግል ማርያም በኢትዮጵያ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ተአምረ ማርያም በሚባለው የጸሎት መጽሓፍ ቅድስት ድንግል ማርያም በማቴዎስ ወንጌል እንደተጻፈው በሕፃንነቱ ልጇን ጌታ ኢየሱስን እንዳይገድሉባት ከምድረ እስራኤል ስትሸሽ በግብጽ አልፋ ወደ ኢትዮጵያ ምድር ደርሳለች። ጌታ ኢየሱስ በእግሩ በመረገጡ ከእናቱ ከድንግል ማርያም ከአረጋዊው ከቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ ከዘመዳቸው ከቅድስት ሰሎሜ ጋር በእንግድነት በመቀመጡ ምድረ ኢትዮጵያን ባርኳታል። እመቤታችንን በጭንቀቷ ሰዓት ይቺ ምድርና ሕዝቦቿ ስለተቀበሏት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአደራነት ወይም በአሥራትነት ኢትዮጵያን ለቅድስት ድንግል ማርያም እንደሰጣት ቤተ ክርስቲያኒቷ ታስተምራለች።


በዚህ ምክንያት በኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ዘንድ እጅግ በጣም ልዩ ተወዳጅነትና ፍቅር ያላት በተለምዶ እንኳን እምዬ እናታችን እመቤታችን ወይም በመዓረግ ስሞቿ ኪዳነ ምሕረት ወላዲተ አምላክ እመብርሃን ተብላ ትጠራለች። ከኃይማኖትም ባሻገር በኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ባህልም ቅድስት ድንግል ማርያም ልዩ ቦታ አላት። ለምሳሌ አንዲት እርጉዝ ሴት ልትወልድ ስትል «ድንግል ማርያም ትቅረብሽ» ስትወልድም «እንኳን ማርያም ማረችሽ» በአራስ ቤትም ሳለች «ድንግል ማርያም በሽልም ታውጣሽ» ትባላለች። አንድ ሰው ገላው ላይ ሲወለድ የነበረ ጥቁር ምልክት ቢኖረው «ድንግል ማርያም እዚህ ስምሃለች» ይባላል።

ፍልሰታ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ጾመ ፍልሰታ
የእመቤታችን እርገቷ

ፍልሰታ የሚለው ቃል የሚገልጸው ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለቆ መሔድን መሰደድን መፍለስን ያመለክታል። ይህም የእመቤታችንን ሥጋ ከጌቴሴማኒ ወደ ገነት መፍለሱን በኋላም በገነት በዕፀ ሕይወት ስር ከነበረበት መነሳቱን ለማመልከት ይነገራል።

ጾመ ፍልሰታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፷፬ ዓመት በዚች ምድር ኖራ እንደ አንድ ልጇ መሞቷን መነሳቷንና ማረጓን ያዩ ዘንድ ሐዋርያት የጾሙት ጾም ነው። ጾሙ ከነሐሴ 8 ቀን አስከ

ነሐሴ ፲፮ ቀን ሲጾም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአዋጅ ከደነገገቻቸው ሰባቱ አጽዋማትም አንዱ ነው።

ኃይማኖታዊ መሠረት

እመቤታችን ከአባቷ ከኢያቄም እና ከናቷ ከሐና ነሐሴ ፯ ቀን ተጸንሳ ግንቦት ፩ ቀን በሊባኖስ ተወልዳለች# <እምሊባኖስ ትወጽዕ መርአት : ከሊባኖስ ሙሽራ ትወጣለች > እንደተባለ ። እምቤታችን በእናት አባቷ ቤት ሦስት ዓመት፤ በቤተ መቅደስ አሥራ ሁለት ዓመት፤ ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር : hዮሐንስ ወልደዘብዴዎስ ዘንድ አሥራ አራት ዓመት ከዘጠኝ ወር ቆይታ በ ፷ä ዓመት ዕድሜዋ በ፱ ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች። የእመቤታችንን ስም የሚገልጹ የውዳሴ ጽሑፎችም በእድሜዋ ልክ ተደርሰዋል። ለምሳሌ የውዳሴ ማርያም ቁጥር ፰ö ነው የመልክአ ማርያም ቁጥርም ፷ö ነው።

ባረፈች ጊዜ ቅዱሳን ሐዋርያት ተሰባስበው አስከሬኗን ይዘው ወደ ጌቴሴማኒ መቃብር ለማሳረፍ ሲሄዱ አይሁድ ለተንኮል አያርፉምና ተተናኮሏቸው። ቀድሞ ልጇ ሞቶ ተነሳ፣ አረገ እያሉ ሲያስቸግሩን ይኖራሉ፡ ደግሞ አሁን እሷም ተነሳች፣ አረገች ሊሉ አይደል በማለት አይሁድ ተሰባስበው አስከሬኗን ለማቃጠል ሲተናኮሉ እግዚአብሔር በተአምር ከነዚያ አይሁዶች አድኗቸዋል :: የእመቤታችንንም አስከሬን ነጥቆ ከሐዋርያው ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር በገነት በዕፀ ህይወት ስር አኑሯቸዋል ። ከዚያ በኋላ ሐዋርያት ሥጋዋን አግኝተው ይቀብሩት ዘንድ በአረፈች በስምንተኛው ወር ከነሐሴ ፩ ጀምሮ Aስከ ነሐሴ ፲ ቀን ድረስ ሁለት ሱባዔ ይዘው በአሥራ አራተኛው ቀን ሥጋዋን ከጌታ ተቀብለው በጸሎትና በምህላ በፍጹም ደስታ በጌቴሰማኔ አሳረፉት ። በ ሦስተኛውም ቀን ተነስታ ስታርግ ከሰኡቃዊያን ወገን የሆነው ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ አያት። እርሱም በቀብር ስርዓቱ ጊዜም አልነበረም። ሀገረ ስብከቱ ህንድ ስለነበር ሊያስተምር ወደዛው ሂዶ ነበርና። በዚያም ሲያስተምር ሰንብቶ በደመና ተጭኖ ሲመጣ ያገኛታል። ትንሳኤዋን ከርሱ ሰውራ ያደረገች መስሎት አዝኖ «ቀድሞ የልጅሽን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንቺን ትንሳኤ ሳላይ ቀርቼ ነውን ?» ብሎ ቢያዝንባት እመቤታችንም ከርሱ በቀር ማንንም ትንሳኤዋን እንዳላየ ነግራ አጽናናችው። ለሌሎቹ ሐዋርያትም እንዲነግራቸው ለምልክትም /ለምስክርም እንዲሆነው ሰበኗን /መግነዟን ሰጥታው አረገች። ቶማስም ኢየሩሳሌም ደርሶ ሐዋርያትን የእመቤታችን ነገርስ እንደምን ሆነ?» ሲል ቢጠይቅ «አግኝተን ቀበርናት እኮ» አሉት። እርሱ ምስጢሩን አዉቆ ደብቆ «ሞት በጥር በነሐሴ መቃብ» እንዴት ይሆናል ? አይደረግም ይላቸዋል። ሊያሳያቸውም መቃብሩ ዘንድ ሂደው ቢከፍቱት አጧት። እርሱም «አታምኑኝም ብዬ እንጂ እርሷስ ተነስታ አርጋልች» በማለት ሁኔታውን ተረከላቸውና ለምስክር ይሁንህ ብላ የሰጠችውን ሰበኗን አሳያቸው። ከዚህ በኋላ ለበረከት ይሆናቸው ዘንድ ሰበኑን ተካፍለው ወደየአህገረ ስብከታቸው ሄዱ። ዛሬ በቅዳሴ ጊዜ ዲያቆኑ በሚይዘው የመጾር መስቀል ላይ በሁለት ቀዳዳዎች አልፎ ተጠምጥሞ የምናየው መቀነት መሰል ጨርቅ የዚያ ሰበን ምሳሌ ነው።

በዓመቱ ሐዋርያት ከያሉበት ተሰባስበው ቶማስ ትንሳኤሽን አይቶ እኛስ እንዴት ይቀርብናል ብለው ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምርው ሱባዔ ቢይዙ ከሁለት ሱባዔ በኋላ እንደገና ትንሳኤዋንና እርገቷን ለማየት በቅተዋል። ሐዋርያዊት የሆነች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናም ምእመኖቿ ከእመቤታችን በረከትን እንዲያገኙ ይጾሙ ዘንድ ይህን ሐዋርያት የጾሙትን ጾም እንዲጾሙ አዉጃለች። ምእመናንም በተለየ መልኩ በጾም በጸሎት በሱባዔ ጽሙድ ሆነው ይህን ወቅት ያሳልፋሉ።

የእመቤታችን ትንሳኤ ድንገት እንደእንግዳ ደራሽ እንደ ዉሀ ፈሳሽ የተደረገ ሳይሆን በቅዱሳት መጻሕፍት በትንቢተ ነቢያት የተገለጸ ነው። ነቢዩ ዳዊት በመዝሙር ፻፴፩ ቁጥር ፲ ላይ «አቤቱ ወደ እረፍትህ ተነስ አንተና የመቅደስህ ታቦትም» ይላል። በዚህም ምዕመናንን ወደ ምታሳርፍበት ወደ መንግሥተ ሰማያት የመቅደስህ ታቦት ድንግል ማርያምን ይዘህ ተነስ አለ። ታቦት የጽላት ማደርያ እንደሆነ ሁሉ እምቤታችንም ለክርስቶስ ማደርያ በመሆኗ አማናዊት ታቦት ትባላለች።

ንጉስ ሰሎሞንም በመኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ምዕራፍ ፪ ቁጥር ፩ ላይ «ውዴ እንዲህ ብሎ ተናገረኝ፤ ወዳጄ ሆይ ተነሽ፡ ውብቴ ሆይ ነይ» ብሏል። እዚህ ላይ ወዳጄ ...ዉበቴ»" የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት # ክቡር ዳዊት መዝሙር ö ቁጥር ፱ ላይ «በወርቅ ልብስ ተጎናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች» እንደሚል ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛነቱን ከፈጸመ በኋላ ወደ ቀደመ ክብሩ እንዳረገ እመቤታችን ቅድስት ድንገል ማርያምም በቀኙ ትቀመጥ ዘንድ «ተነሽ ነይ» አላት ። እንግዲህ ይህንና የመሰለዉን ሁሉ ይዘን የእናታችንን እረፍቷን ትንሳኤዋን እንዘክራለን እንመሰክራለንም።

እስልምና[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የማርያምን ድንግል ሁና እየሱስን ወይንም እነሱ እንደሚሉት ኢሳ (አ.ሰ)ን እንደወለደች ብሎም በነሱ እምነት አራት ተብለዉ ከተጠቀሱ ምርጥ ሴቶች ዉስጥ አንድዋ ነች። ነገር ግን ኢሳን የአላህ መልዕክተኛ ነዉ ሲሉት፣ አላህም ፈጣሪዉ እንጅ ልጁ አይደለም ባዮች ናቸው። በቁርአን ምክንያት አምላክ አይወልድም አይወለድም፤ ይህም ለአላህ የማይገባው ሥራ ነው ይላሉ።

ሥዕሎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

«ምስለ ፍቁር ወልዳ» የሚባለው ሥዕል ልጇን ጌታ ኢየሱስን አቅፋ ቅዱሳን መላእክት ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል (መልዐክ) ግራና ቀኝ ቆመው
ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታ ኢየሱስን ይዛ ወደ ኢትዮጵያና ኤርትራ ተሰዳ እንደመጣች የሚገልጽ ሥዕል
በኢትዮጵያ ውስጥ አለች የምትባለው ገዳም ለቅድስት ድንግል ማርያም ስምና ክብር የተሠራች የአክሱም ፅዮን ቤተክርስቲያን።

ማጣቀሻ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

መደብ:በክርስትና ማርያም ታማልዳለች አታማልድም

  1. ^ በአንተና፡በሴቲቱ፡መካከል፥በዘርኽና፡በዘሯም፡መካከል፡ጠላትነትን፡አደርጋለኹ፤ርሱ፡ራስኽ ን፡ይቀጠቅጣል፥አንተም፡ሰኰናውን፡ትቀጠቅጣለኽ።
  2. ^ በኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች
    በካቶሊክ ክርስቲያኖች
    በእስልምና