ቁርአን

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
የተዋበ የቁርአን ሽፋን

ቁርዓንእስልምና ትምህርትና እምነት ዘንድ የአላህ ቃል (ንግግር) ነው። በነብዩ መሀመድ አማካኝነት ለመላው የሰው ልጅ ነብይ እና መላክተኛ ሆነው ህዝቦች አንድ አምላክን ብቻ እንዲያመልኩ ለማስተማር ሲላኩ መመሪያቸው ቁርአን ነበር። ይህ ቁርአን ያለፉትን ህዝቦች ታሪክ የያዘ የሚመጣውን ነገር የሚተነብይ፡ የሰዎች ማህበራዊ እና መንፈሳዊ ህይወታቸው ምን መሆን እንዳለበት የሚያስተምር የተሟላ ቅዱስ መጽሃፍ ነው።

ቁርአን ሰዎች እና አጋንንት እንኳ ቢሰበሰቡ የሱብ ተመሳሳይ አንቀጽ ወይም አረፍ ተነገር ማምጣት ይችሉ እንደሆነ ይሞክሩ በማለት ተአምረኛነቱን እና እውነተኛነቱን አረጋግጧል። ቁርአን ከመበዘረዝ እና ከመከለስ የጠራ ነው። እንደዚህም የሰው ልጆች ሁሉ መመሪያ እንደሆነ ሳይበረዝ እና ሳይከለስ እስከ ትንሳኤ ቀን ድረስ ይቆያል፤ ምክንያቱም አላህ እጠብቀዋለሁ ብሎ ቃል ስለገባለት ቁርአንን በተመለከተ ሙስሊሞች ምንም አይነት ልዩነት የለባቸውም። በአረብኛ ተጽፎ አንድ ቃል ይቅርና አንድ ፊደል እንኳ ሊጨመር ቢችል ወይም ቢቀነስ በቀጥታ በቀላሉ ማወቅ ይቻላል። የሰው ልጆች በዚህ ምድርም ይሁን በመጭው አለም ሰላም እና እርጋታ ከፈለጉ ሙስሊም ሆነው በቁርአን መመራት አለባቸው የሚል ትምህርት ያቀርባል።

የውጭ መያያይዣ[ለማስተካከል]