የካቲት ፲፮

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

የካቲት ፲፮፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፷፮ ኛው ዕለት ሲሆን፤ የበጋ ወቅት ፶፩ ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፪፻ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፺፱ ቀናት ይቀራሉ።

ማውጫ

ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች [ለማስተካከል]

  • ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በግራትዚያኒ የሚመራ የፋሺስት ኢጣልያ ሠራዊት በዝዋይ አካባቢ የጦር አዝማቾቹን የራስ ደስታ ዳምጠውን እና የደጃዝማች በየነ መርዕድን አርበኞት ድል አደረጉ። ሁለቱም ኢትዮጵያውያን አዝማቾች ሕይወታቸውን በዚህ ዕለት ሰዉ። ኢጣሊያውያኑ ራስ ደስታን ከያዟቸው በኋላ በጥይት ደበደቧቸው፡፡
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም ኢትዮጵያ ላይ በፈነዳው አብዮት አስገዳጅነት የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የሕዝቡን ሸክም ለማቃለል የነዳጅ ዋጋ ቅነሳን የሚያካትት ኤኮኖሚያዊ እርምጃዎችን እንደሚወስድ ይፋ አደረገ።


ልደት [ለማስተካከል]

ዕለተ ሞት [ለማስተካከል]

  • ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - የግራዚያኒ ሠራዊት በአሩሲና በማረቆ ላይ ትልቅ ጦርነት አድርጎ፣ ራስ ደስታ ዳምጠው እና አብረዋቸው የነበሩትን የጦር አለቆች ማርኮ በዚህ ዕለት በፋሺስቶች እጅ ተገደሉ። [1]

ማጣቀሻ [ለማስተካከል]

  1. ^ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ (፲፱፻፷፭ ዓ/ም)፤ ገጽ ፪፻፲፭

ዋቢ ምንጮች [ለማስተካከል]


የኢትዮጵያ ወራት
መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ