ሊኑክስ

ከውክፔዲያ
የሊኑክስ ምልክት

ሊኑክስ የሚባለው ቴክኖሎጂ የኮምፒውተር ዉስጠ-አካልን የሚቆጣጠር (ስርአተ ክውና) ዩኒክስን የሚመስል ሶፍትዌር ነው። ነገር ግን ብዙ ጊዜ ሰዎች ሊኒክስ ብለው የሚጠሩት ከዩኒክስ የሚባለው ኦፕሬቲንግ ሲስተም የተወለዱትን ኦፕሬቲንግ ሲስተሞችን ነው።

ሊኑክስ በነፃ ከሚገኙ ሶፍትዌሮች ግንባር ቀደም ተብሎ ሊጠቀስ የሚችል ነው። የምንጭ ኮድንም ማለትም ሊኑክስ የተጻፈበትን ኮድ ተጠቃሚው ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ሊቀይረው፣ ሊጠቀመው ብሎም እንደገና ሊያሰራጨው ይችላል። የሊኑክስ ከርነል ለመጀመሪያ ጊዜ በ17 ሴፕቴምበር 1991 እ.ኤ.አ. ለህዝብ ቀረበ። ይኸውም ለኢንቴል x86 ፒሲ አርክቴክቱር የተሰራው ነበር። ከዚሀም በተጨማሪ ከርነሉ ጠቃሚ ስርአተ ክወና እንዲሆን ከጂኤንዩ ፕሮጀክት በላይብራሪዎችና በሲስተም ዩቲሊቲዎች የታገዝ ነበር። ቆይቶም ጂኤንዩ/ሊኑክስ የሚለውን ስም ተሰጥቶታል። ሊኑክስ በአመዛኙ በሰርቨሮች ውስጥ ባለው ጥቅም ይታወቃል በመሆኑም ከአይቢኤምሰን ማይክሮሲስተምስዴልሄውሌት ፓካርድኖቬልን ከመሳስሉ ድርጅቶች እርዳታን ሲያገኝ ቆይቶአል። ከዚሀም በተጨማሪ ሊኑክስ በተለያዪ የኮምፕዩተር ቁሥ አካላት ላይ ማለትም ሃርድ ዌር፣ በዴስክ ቶፕ ኮምፒዩተሮች ላይ፣ በምጡቅ ኮምፒዩተርዎች ማለትም ሱፐር ኮምፒዩትር ላይ ፣ በኢምቤድድ መሳሪያዎች፣ በሞባይል ስልክዎችና በራውተርዎች እንደ ስርአተ ክወና ሆኖ ያገለግላል።

ሊኑክስ በአሁኑ ሰአት ለተለያየ ጥቅም በአካታች ውስጥ ገብቶ ማለትም «ፓኬጅድ ሆኖ» በስርጭት ላይ ይግኛል። በዚህም ምክንያት ከርነሉ በጥቂቱ ተቀያይሮ እንገኘዋለን።

ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ubuntu

ሊኒክስን የፈጠረው ሊኑስ ቶርቫልድስ የሚባል የፊንላንድ ዜጋ ነው። የዩኒክስ ስርአተ ክወና የተጸነሰውና የተገበረው በ1960 እ.ኤ.አ. ከዛም በ1970 እ.ኤ.አ. ተለቀቀ። በሰፊው መገኘቱና እንዲሁም ተጓጓዥንቱ ማለትም ፖርተብሊቲው በተለያዩ የትምህርትና የንግድ ተቋምት እንዲራባ፣ እንዲቀየር ብሎም በሌሎች ስርአት ክወናዎች ላይ የዲዛይን ተጽኖ እንዲያመጣ አስችሎታል።