ሜሪ አርምዴ

ከውክፔዲያ

ሜሪ አርምዴኢትዮጵያ ታዋቂ ዘፋኝ ስትሆን ባህላዊ ዘፈኖችን በወፈረ ድምጽ በማቅረብ ትታወቃለች። ማርታ አሻጋሪም ከሜሪ አርምዴ ጋር ተመሳሳይ ድምጽ እንዳላት ይነገራል።

የህይወት ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ሜሪ አርምዴ

----------------

-

ቤተሰቦቿ ያወጡላት ስም ሜሪማ የሚባል እንደነበር ይነገራል፡፡ ኋላ ላይ ዘመናዊነትን ስትነግሥበትና ፒያሳን ስትደምቅበት በራሷ ጊዜ ስሟን ሜሪ ብላ አስተካከለቸው፡፡

-

ሜሪ የተወለደችው በ1910 ዓ. ም.  በአዲስ አበባ ከተማ ዶሮ ማነቂያ ከሚባለው ሰፈር ነው፡፡

-

ቤተሰቦቿ ፈረንሳይኛን የተማሩ ሲሆኑ በፈረንሳይ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ውስጥ ይሰሩ እንደነበር ሜሪ በ1973 ዓ. ም.  ለኢትዮጵያ ሬዲዮ በሰጠችው ቃለ መጠይቅ ላይ ተናግራለች፡፡

-

ምክንያቱ ባይታወቅም ሜሪ ገና በልጅነቷ አዲስ አበባን ለቃ ወደ ራያ ኮረም የሚባል ቦታ ሄዳለች፡፡ የልጅነት ጊዜዋንም በዚያው አሳለፈች፡፡

-

ፋሺስት ጣሊያን ኢትዮጵያን ሲወር ሜሪ የ13 ዓመት ልጅ ነበረች፡፡ መዝፈን፣ ማንጎራጎርም በዚያ ወቅት ጀምራለች፡፡

-

አምባላጌ ላይ የኢትዮ - ጣሊያን ጦርነት ሲጧጧፍ ሜሪ ብላታ ኅሩይ ከተባሉ አርበኛ ጋር አብራ ዘምታ ነበር፡፡

-

የአምባላጌውን እልህ አስጨራሽ ጦርነትን ጨምሮ ሌሎችም በአርበኞችና ፋሽስት ጣሊያን መካከል የሚደረግን ፍልሚያ በቅርበት አይታለች፡፡

-

በአንድ አውድ ላይም እግሯን ተመትታ የጦርነትን ዋጋ ከፍላለች፡፡ በዚህ ሁሉ ውስጥም ግን በእንጉርጉሮ ፣ በዘፈንና ሽለላዋ የአርበኞቹ የደስታ ምንጭ ነበረች፡፡

1. ዘመናዊ ዳንስ

2. ዘመናዊ የልብስ ስፌት

3. የፀጉር ተኩስ ስራ  ሙያዎች

በአዲስ አበባ ሜሪን ቀደምትና ታዋቂ አድርገዋታል ፡፡

-

በዚያ ላይ ታንጎራጉራለች፣ ክራር ትጫወታለች፣ የዳንስ ቤት ከፍታለች፡፡  በወቅቱ ስላልተለመደ ብዙዎች ባይወዱላትም የፀጉር ተኩስ ስራን ለብዙዎች ቀስ በቀስ እንዲወዱትና እንዲለምዱት አድርጋለች፡፡ በዚህም ሜሪ በከተማው ዝናዋ የናኘ ነበር፡፡

የስራ ዝርዝር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ማጣቀሻወች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]