ሮመስ

ከውክፔዲያ
                የበረሃው ጉዞ{1}

ለህይወት ዋጋ ስጥ

   ለህይወት ዋጋ ስጥ ዛሬ የተባለው
   የፈጣሪ ትዛዝ ከአዳም ጀምሮ ነው

አሁንም የሰው ልጅ ህግም ዓያግደው ሁሌም ተሸናፊ ለደካማ ስጋው

አዳም የተሰጠው ያመልካም ሕይወት
እንዲኖር ነበረ ባምላክ በረከት
ሁሌም ተንደላቆ በገነት ለመኖር
በተሰጠው ጸጋ በሃሴት በፍቅር
አምላክ ህግ ሰጠው እንዲኖር ከሱ ጋር
  የፈጣሪን ፈቃድ አዳምም ረስቶ 
  የህይወቱን ዋጋ በፍሬ ተክቶ 

ቢበላት ተሻረ ፍሬዋን ቀን ጥሶ ጸጋው ተገፎበት አተረፈ ለቅሶ

ለህይወት ዋጋ ስጥ ብሎ ያለው አምላክ
አሁንም ይለናል ዓረ እንኑር በልክ

የሰው ልጆች ህይወት ያለው በደም ስር ነው የመኖሩ ጸጋ ካምላክ የተሰጠው እስትንፋስን ሁሉ የሚቆጣጠረው የህይወት ዋጋችን ደማችን እኮ ነው አየር ምግባችንን ይዞ የሚዞረው

  ባለም መኖራችን በደም ነው በደም ነው
  የአምላካችን ጸጋ ህይወት የሚያድነው

ህጉን በመጠበቅ እንክፈለው ዋጋ መቅበዝበዝ ይቅርብን እዚም ጋር እዚያ ጋ ይለናል ፈጣሪ እንኑር ከእኔ ጋ!!!!

  ተጻፈ በወርሃ ክረምት 1995 እኢአ