Jump to content

ሲሳይ ንጉሱ

ከውክፔዲያ

ሲሳይ ንጉሱ በ1951 ዓ.ም. አዲስ አበባ የተወለዱት ሲሳይ ንጉሡ አንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በባልቻ አባነፍሶ፣ የሁለተኛ ደረጃን ደግሞ በአዲስ ከተማ አጠቃላይ ተከታትለዋል፡፡ የከፍተኛ ትምህርታቸውን በአሥመራ ዩኒቨርሲቲ ከ1974 -1977 ዓ.ም. ድረስ ተምረዋል።

በዩኒቨርሲቲ ሕይወት ዙሪያና በፍቅር ታሪክ ላይ በሚያተኩረው ሰመመን በሚባለው መጽፈሐፍቸው በብዙዎች ዘንድ የታወቁት ሲሳይ ንጉሡ፣ ጉዞው፣ ግርዶሽ፣ የቅናት ዛር የተባሉ ረጃጅም ልብወለዶች አሏቸው፡፡ ጉዞው የሚለውን ኖቬላ ጨምሮ ሌሎች አጫጭር ልብወለዶችን ጽፈዋል፡፡ ከኢትዮጵያ ሥነ ጥበባትና መገናኛ ብዙኃን ሽልማት በሥነ ጽሑፍ ዘርፍ ተሸላሚም ሆነዋል፡፡ ቀደም ባሉት ጊዜያት የደራሲያን ማኀበር ዋና ጸሐፊ በመሆን አገልግለዋል፡፡ ልቦለድ ከመጻፋቸው በላይ ለሩህ መጽሔት አዘጋጅ ሁነው ይሠሩ ነበር። እንዲሁም የኢትዮጵያውያን ጸሐፊዎች ማህበር ሊቀ መንበር ሆነዋልም አገልግለዋል።

የመጽሐፍ ስም የሕትመት ዘመን
Sememen book by Sisay Nigusu
ሰመመን
ሰመመን 1985 እ.ኤ.አ.
  • ሰመመን (1985 እ.ኤ.አ.)
  • ግርዶሽ (1989 እ.ኤ.አ.)
  • ትንሣኤ
  • የቅናት ዘር (1988 ዓ.ም.)
  • ረቂቅ አሻራ (1995 ዓ.ም.)