Jump to content

ቀንጠፋ

ከውክፔዲያ
ቀንጠፋ

ቀንጠፋ ወይም ቆንጥር (Pterolobium stellatum) ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው።

የተክሉ ሳይንሳዊ ጸባይ

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ሌላ ዝርያ፣ የግራር ዛፍ አይነት Acacia brevispica ደግሞ «ቀንጠፋ» ተብሏል።

ሁለቱም በአተር አስተኔ ወይም «አባዝርት» አስተኔ ናቸው።

በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በምሥራቅ አፍሪካና በየመን ይገኛል። በድንጋያማ ዳገት፣ በወንዝ ደለል፣ በጫካ ዳርቻ ይገኛል።

የተክሉ ጥቅም

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ለቊጥቋጦ-ኣጥር ይስማማል። ቡቃያዎቹም ለከብት መኖ ይሰበሰባሉ።

በኢትዮጵያ፣ የተደቀቀው ልጥ ጭማቂ በቆዳ ፋቂ ለማቀላት ተጠቅሟል።[1] ቅጠሎቹም ሲደቀቁ ጨለማ-ቀይ ቀለም ይሠራል።

ትኩስ ቅጠሎቹ ለመድሃኒት ይኘካል፣ ለምሳሌ የሳምባ ነቀርሳን ወይም ተመሳሳይ የመተንፈስ ችግሮችን ለማከም።[2]

የቀንጠፋው ፍሬ ለማስታወክ እንደሚጠቀም ተዘግቧል።[3]

  1. Jansen, P.C.M. & Cardon, D. (2005). Dyes and Tannins. Plant resources of tropical Africa. 3. Prota. pp. 134–135.
  2. አማራ ጌታሁን - SOME COMMON MEDICINAL AND POISONOUS PLANTS USED IN ETHIOPIAN FOLK MEDICINE Archived ጁላይ 31, 2017 at the Wayback Machine March 1976 እ.ኤ.አ.
  3. የፍቼ፣ ኦሮሚያ ባህላዊ መድሃኒት ጥናት 2006 ዓም ከዓቢዩ እኒየው እና ሌሎች፣ ጎንደርና አዲስ አበባ ኡኒቨርሲቲዎች ሥነ ፍጥረት ኮሌጆች