ቃታ መፈልቀቂያሽን

ከውክፔዲያ

ቃታ መፈልቀቂያሽን

(62)ሴትዮዋ ድምጽ ሳይሰማ ማስተንፈስ ፈለጉና በጣታቸው አንድ መቀመጫቸውን ከፈት አድርገው ቢለቁት ሳይሳካላቸው ቀርቶ ዱጥ ቢልባቸው ደንግጠው «ደራን ወጋው» ይሉና ዞር ሲሉ አለቃን ያዩዋቸዋል። ከዛም “አለቃ መቼ መጡ?” ብለው ቢጠይቋቸው «ደራ የተወጋ ጊዜ» ብለው ይመልሱላቸዋል። ሴትዮዋም በመደንገጥ «ምነው ጣቴን በቆረጠው?» ቢሉ አለቃም ቀበል አድርገው «ተይ እንጂ ምነው ቃታ መፈልቀቂያሽን» አሏት አሉ፡፡