በር:ፍልስፍና/የተመረጠ ጽሑፍ/39

ከውክፔዲያ

ጥገኛ አምክንዮ


ጥገኝነት የሚፋለሰው A እውነት ሆኖ B ውሸት ሲሆን ብቻና ብቻ ነው። ከላይ ባለው ቬን ምስል ይህ የውሸት ክፍል በነጭ ቀለም ተለይቶ ይታያል።
ጥገኝነት በሂሳብ ትርጓሜው እንዲህ ይሰፍራል

A → B ¬A B
የጥገኝነት አምክንዮን የሚተገብር የማብሪያ ማጥፊያ ትልም

ጥገኛ አምክንዮ በሁለት የአምክንዮ ዋጋወች የሚተገበር ሲሆን፣ ውጤቱ ውሸት የሚሆነው ቀዳሚ አረፍተ ነገሩ እውነት ሁኖ ተከታይ አረፍተ ነገሩ (ጥገኛ አረፍተ ነገሩ) ውሸት ሲሆን ብቻና ብቻ ነው። (ቀዳሚና ተከታይ አረፍተ ነገር ምን ማለት እንደሆነ ከታች ሙሉ ማብራሪያ የሚለውን ክፍል ይመልከቱ ) ከአምክንዮ አንጻር ጥገኛ አምክንዮ ከአይደለም....ወይም... ጋር እኩል ነው። በሂሳብ አጻጻፍ፣ p ቀዳሚ አረፍተ ነገር (አስጠጊ) ቢሆንና q ተከታይ (ጥገኛ) ቢሆን፣ የጥገኝነት ዝምድናቸው እንዲህ ይጻፋል p → q ፡ ሲነበብ p ስለዚህ q ነው። ይህ እንግዲህ ከላይ እንደተጠቀሰው ከ አይደለም p ወይም q ጋር ምንም ለውጥ የለውም። ይህን የመጨረሻውን ግኝት

በምሳሌ እንይ፡

መሰረት አዲስ አበባ ውስጥ ናት፣ ስለዚህ መሰረት ኢትዮጵያ ውስጥ ናት

ከላይ በጻፍነው ትርጓሜ አንጻር ሲተረጎም

መሰረት አዲስ አበባ ውስጥ አይደለችም ወይም መሰረት ኢትዮጵያ ውስጥ ናት

ከላይ የተጻፉትን አረፍተ ነገሮች አነጻጽረው እኩለነታቸውን ያረጋግጡ