በር ውይይት:ፍልስፍና

Page contents not supported in other languages.
ከውክፔዲያ

ስለ ፍልስፍና ስናወራ አንድ መታወስ ያለበት ነገር አለ። ይኽውም የታወቁት ፈላስፎች ትምህርታቸውን የገበዩት ድሮ ኢትዮጵያ ከምትባለው ማለትም አሁን አፍሪካ የሚባለው የአለም ክፍል አጠቃሎ እነዲሁም አብዛኛውን የአረቦች የሚኖሩበትን አለማትን ጨምሮ ነው። ስለዚህ ፊሎዞፊ ይሚለውን ቃል ሊያገኙት የቻሉት ከእኛው ከኢትዮጵያኖች ዘንድ ነው። ከዛም አልፎ ይኽ ቃል ከግሪክ ሳይሆን ከግዕዝ ነው የተገኝው። በእድሜም በኩል ብናስተያይ ግዕዝ መፃፍ የተጀመረው ተብሎ የሚታመነው ከ6000 ዓመታት ከክርስቶስ ልደት በፊት ሲሆን የግሪኩ ደግሞ ከ500 ዓመታትን ብቻ ነው ያለው። የግሪኩም ፈላስፎችም ሳይቀሩ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁት ኢትዮጵያ እንደሆነ ሳይደብቁ በመጽሃፎቻቸው አስፍረውታል። ለምሳሌ ያኽል ለመጥቀስ፦ ፓይታጎረስን ማንሳት እንችላለን። ፓይታጎረስ ትምህርቱን ይከታተል የነበረው ለ22 ዓመታት ያህል በምስርያን (በግብፅ) ነበር። እውነትን እንናገር ካልን ፒራሚዶቹ ተሰርተው ያለቁት ፓይታጎረስ ከመዎለዱ ከብዙ አመታት በፊት እንደሆነ ታሪክ ይነግረናል። እነዚህ የአለምን ትንግርትን የሳቡ ትላልቅ የሆኑ ህንጻዎች የተገነቡት እንደ ፓይታጎሪያን የመሳሰሉ ፎርሙላዎችን በመጠቀም ነው። ነገር ግን ይኽን የመሰሉ ስራዎች ምስጋናን የሚያገኙት ሌላው አካል ሲሆን የኛ አባቶቻችን የፈጠሩት ስራውች ግን ከራሳቸው ተወስዶባቸዋል። ከዚህም በተጨማሪ የሚቀጥለውን ሊንክ ይመልከቱ። የተሰረቀው ለጋሲ