በቁሜ ቀምሼ መጣሁ

ከውክፔዲያ

በቁሜ ቀምሼ መጣሁ

(46)አለቃ ድግስ ተጠርተው አረፋፍደው ድግስ ቤቱ ቢደርሱ ሰዉ ሁሉ ተሳክሮ በብርሌ ሲፈነካከት ይደርሳሉ። ገና በሩን ገባ ከማለታቸው አንድ የተወረወረች ብርሌ ግንባራቸውን ትላቸዋለች። አይ ከዚህስ ቢቀርብኝ ይሻላል ብለው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ አንድ የሚያውቁትን ሰው መንገድ ላይ ያገኛሉ። ሰውየው «አለቃ ድግሱ እንዴት ነበር?» አለቃም «በጣም ቆንጆ ነበር። ቶሎ ሂድ እንዳያመልጥህ እኔ እንኳን አንድ በቁሜ ቀምሼ መጣሁ» ብለውት እርፍ።