በጠማማ ቁና ሁለት ሁለት (1)(2)

ከውክፔዲያ

በጠማማ ቁና ሁለት ሁለት (1)

(49)አለቃ ምግብ በተልባ በልተው አፋቸውን ሳያብሱ አደባባይ ወጥተዋል። አንዲት የተልባ ቅንጣት ወደ አገጫቸው ተለጥፋ ኖሯለች።አንድ ተጫዋች ወዳጃቸው አለቃ «ዛሬ ተልባ ስንት ስንት ዋለ?» ብሏቸዋል። አለቃም ገብቷቸው ስለነበረ ሰውየው የኔ ብጤ ውልግድግድ ያለ ስለነበረ «በቅፅበት በጠማማ ቁና ሁለት ሁለት ዋለ» አሉት አሉ።

በጠማማ ቁና ሶስት ሶስት (2)

(50)አለቃ ገብረሀና የኢትዮጵያ ዘመናዊ ጥበበ ቀልድ /ኮሚዲ መስራች ሊባሉ ይገባል። አንዳንድ ተቺ ሰው አለ አይደል ዝም ብሎ መተቸት የሚወድ አይነት። አለቃ የበሉት ተልባ አፋቸው ላይ ሳይጠረግ አይቶ «ተልባ ገበያ ላይ እንዴት ዋለ?» ቢላቸው ሰውየው አፉም እግሩም የተጣመመ ስለነበር «በጠማማ ቁና ሶስት ብር ነበር።» አሉት።