ብርሃኑ ዘሪሁን

ከውክፔዲያ

ብርሃኑ ዘሪሁንኢትዮጵያውያን ደራሲያንና አንጋፋ እውቅ ጋዜጠኞች አንዱ ነው። በደርግ ዘመን እስርና እንግልት የተፈራረቁበት፣ መራራውን የዘመኑን ሥርዓትና ሳንሱር የታገለ ጀግና ነበር። ብርሃኑ ከአሥር በላይ መጻሕፍትን ጽፏል። ከነዚያም መሀል ታዋቂዎቹ ታሪካዊ ልብ ወለዶች፣ «የታንጕት ምስጢር» «ማዕበል ያብዮት ዋዜማ፣ መባቻና ማግስት»፣ የቴዎድሮስ እምባ፣ ጨረቃ ስትወጣ፣ አማኑዔል ደርሶ መልስ፣ ይገኙበታል። ባልቻ አባነፍሶ፣ ጣጠኛው ተዋንያንና ሌሎችንም ድንቅ ተውኔቶችንም ደርሶ አልፏል።