ብርብራ

ከውክፔዲያ

ብርብራ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው።

የተክሉ ሳይንሳዊ ጸባይ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

አስተዳደግ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

እስከ 12-15 ሜትር ድረስ በቶሎ የሚበቅል ዛፍ ነው።

በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በጫካ ዳር በሰፊ በኢትዮጵያ ይገኛል።

የተክሉ ጥቅም[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

መልካም የማጌጫ ዛፍ ነው።

አሣ መርዝ መሆኑ በሰፊ ይታወቃል። ልጡና የበሰለው ፍሬ ከነዘሮቹ እንደ ዱቄት ተደቅቀው በውሃው ላይ ይበተናል። አሣው ተደንዝዞ ወደ ላይ ሲመጣ ማጥመድ ቀላል ይሆናል።[1]

በሌላ ጥናት ዘንድ፣ የብርብራ ፍሬ ለጥፍ በቅቤ ለሙጃሌ ይለጠፋል። የፍሬውም ዱቄት በማርአሚባ በሽታ ይጠጣል። የቅጠሉ ወይም የአገዳው ጭማዊ ጠብታ በጆሮ ውስጥ ለጆሮ ልክፈት ያክማል። የቅጠሉም ለጥፍ ለጥፍረ መጥምጥ ይለጠፋል።[2]

  1. ^ አማረ ጌታሁን - SOME COMMON MEDICINAL AND POISONOUS PLANTS USED IN ETHIOPIAN FOLK MEDICINE Archived ጁላይ 31, 2017 at the Wayback Machine March 1976 እ.ኤ.አ.
  2. ^ የዘጌ ልሳነ ምድር ባህላዊ መድሃኒት ጥናት 1999 ዓም ከጥላሁን ተክለሃይማኖት፣ ሚሩጸ ጊዳይ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ