ትግራይ ክልል
ትግራይ | |
ክልል | |
![]() | |
የትግራይ ክልልን በቀይ የሚያሳይ የኢትዮጵያ ካርታ | |
![]() | |
ክልል | ትግራይ |
ርዕሰ ከተማ | መቐለ |
የቦታ ስፋት | |
• አጠቃላይ | በግልፅ አይታወቅም[1] |
የሕዝብ ብዛት | |
• አጠቃላይ | 3,201,000[1] |
ትግራይ (በተጨማሪም ትግሬ፣ ትግርኛ) ከ ኤርትራ፣ ሱዳን፣ አማራ ክልላዊ መንግስት እና አፋር ክልላዊ መንግስት ትዋሰናለች። ዋና ከተማዋ መቐለ ሲሆን ከክልሉ ታዋቂ ከተሞች ውቅሮ፣ ዛላምበሳ፣ ዓብዪ ዓዲ፣ ዓድዋ፣ ሓውዜን፥ ሸራሮ፣ ሑመራ፣ ዓዲግራት፣ ኣላማጣ፥ ኮረም፥ አኽሱም፣ ሽረ እንዳስላሰ፣ መኮኒ፣ ማይጨውና ሌሎችም ታዳጊ ከተሞች ይገኛሉ። በ1999 ዓ.ም በተደረገው የቤትና ህዝብ ቆጠራ ግምት መሰረት የክልሉ ህዝብ ቁጥር ከ4.9 ሚልዮን በላይ ይሆናል። የክልሉ ዋነኛ ቋንቋ ትግርኛ ሆኖ ኢሮብኛና ኩናምኛ ቋንቋዎችን የሚናገሩ ህዝቦች ይኖሩበታል። እምባ ኣላጀ፣ ፅበት፣ ሶሎዳ እና ወርሐት በትግራይ ካሉ ከፍተኛ ቦታዎች ይጠቀሳሉ። የትግራይ ክልል በበርካታ ተፈጥሯዊ፣ ታሪካዊ፣ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ሃብቶች የታደለ ክልል ነው። ከ1000 ዓመት ቅድመልደተ ክርስቶስ ጀምሮ የኣክሱም መንግስት እስኪወድቅ የዳኣማት እና ኣክሱም ስልጣኔዎች የታሪክ ኣሻራቸውን ጥለው ኣልፈዋል፡፡ የሓ ጥንታዊ ቤተ መቅደስ፣ የ2500 ዓመት የአክሱም ጥንታዊ ሃውልቶች፣ ከ4ኛው እስከ 18ኛው ክ/ዘመን እንደተሰሩ የሚታወቀው ከ120 በላይ የሚሆኑ ከኣለት ድንጋይ ተፈልፍለው የተሰሩ ውቅር ኣብያተክርስትያናትና ገዳማት እንዲሁም ሌሌች በርካታ ታሪካዊና ኣርኪኦሎጂካዊ ስፍራዎች የሚገኙበት ክልል ነው። ትግራይን በባህልና በታሪካዊ ኣመጣጥ ከኤርትራ እንዲሁም በዛጉዬዎች ከተመራው የአገው ስልጣኔ ነጥሎ ማየት ኣይቻለም።
- ^ ሀ ለ "፳፻፬ ዓ.ም. የትግራይ ብሔራዊ ስታቲስቲክስ". የትግራይ ማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ. Archived from the original on 2015-09-23. በሰኔ ፳፪ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. የተወሰደ.