ኒው ዮርክ ከተማ
Jump to navigation
Jump to search
ኒው ዮርክ ከተማ በሕዝብ ብዛት የአሜሪካ አገር ትልቁ ከተማ ሲሆን 8.4 ሚሊዮን ኗሪዎች ይኖሩበታል። በኒው ዮርክ ክፍላገር ይገኛል።
አውሮፓውያን ከደረሱ አስቀድሞ ጥንታዊ ኗሪዎቹ የለናፔ ወገን ነበሩ። የነሱ ሠፈሮች ካናርሲ፣ ራሪታን፣ ማናሃታ ተባሉ። መጀመርያው የደረሰው አውሮፓዊ በ1516 ዓ.ም. ጆቫኒ ዳ ቬራዛኖ የሚባል ጣልያናዊ ተጓዥ ነበረ። መርከቡ በፈረንሳይ መንግሥት ስም ስለሆነ ስለ ፈረንሳይ ንጉሥ ቦታውን ኑቨል አንጉለም (አዲስ አንጉለም) ሰየመው። ሆኖም አውሮፓውያን መጀመርያ የሰፈሩት የሆላንድ ነጋዴዎች በ1606 ዓ.ም. ነበር። እነርሱ ከ1616 ዓ.ም. ጀምሮ ሥፍራውን ኒው አምስተርዳም (አዲስ አምስተርዳም) አሉት። በ1656 ዓ.ም. እንግሊዞች ያዙትና ስሙን ወደ ኒው ዮርክ (አዲስ ዮርክ) ቀየሩት።
population 8,336,697 (2012)
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |