አሰልበርህት

ከውክፔዲያ
አሰልበርህት

ልበርህት (552 -608 ዓ.ም.) ከ572 ወይም 582 ዓ.ም. አካባቢ እስከ 608 ዓ.ም. ድረስ የኬንት ንጉሥ ነበረ። ከእንግሊዝ ንገስታትም መጀመርያው የተጠመቀ እሱ ነበር። ስለዚህ በሮማ ካቶሊክ፣ በምሥራቅ ኦርቶዶክስና በአንግሊካን ሃይማኖቶች «ቅዱስ» ይባላል።

አንግሎ-ሳክሶን ዜና መዋዕል ዘንድ፣ እሱ አባቱን የኬንት ንጉሥ ኤዮርመንሪክን ተከተለ። የፍራንኮች ንጉሥ ቻሪበርት ልጅ ቤርታን አገባት። እሷ ክሪስቲያን ነበረችና ከዚህ የተነሣ ንጉሥ ተጠምቆ ክርስትና በእንግሊዝ ሕዝብ መካከል ይፋዊ ሆነ። አውግስጢኖስ ዘካንተርቡሪሮማ589 ዓ.ም. ተልከው የእንግሊዝ ሕዝብ መጀመርያ ሊቀ ጳጳስ ሆኑ።

ኤንግላ (አንግሎች) ቀይ፤ ሴያክስ (ሳክሶኖች) ቡናማ፤ ኬንትና አይል ኦፍ ዋይት (ዩቶች) ብጫ

ልበርህት ከኬንት በላይ በዘመኑ መጨረሻ በሌሎች የእንግሊዝ ደሴት መንግሥታት በኤሴክስምሥራቅ ኤንግላ ላይ ገዥነት ነበረው። በእርሱ ተጽእኖ የኤሴክስ ንጉሥ ሳበርህት እና የምስራቅ ኤንግላ ንጉስ ራድዋልድ596 ዓም ግድም ተጠመቁ።

በተጨማሪ በ594 ዓ.ም. ንጉሥ አልበርህት ለአገሩ ሕገ መንግሥት አወጣ። ይህ ሕገ መንግሥት በሮማይስጥ ሳይሆን የተጻፈው በጥንታዊ እንግሊዝኛ ነበረ። በኋላ ዘመን የእንግሊዝ ንጉሥ ታላቁ አልፍሬድ ከዚህ ሕገ መንግሥት ወስደው የተሻሸለ ሕገ መንግሥት አወጡ።

ልበርህት በ608 ዓ.ም. ካረፈ በኋላ ልጁ ኤድባልድ ተከተለው። ኤድባልድ ግን በመጀመርያ ወደ አረመኔነት ቢመልስም በኋላ ግን ክሪስቲያን ንጉሥ ሆነ።

የአሰልበርህት ሕግጋት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

አሰልበርህት ሕግ ፍትሕ ግድያ፣ ስርቆት፣ ዝርፍያ፣ ትግል፣ የሀብት ወይንም የሰውነት ጉዳት፣ ማመንዝር፣ ስላምን ማጥፋት ያደረጉ ሁሉ የገንዘብ መቀጮ ወይም ካሣ ነበረባቸው። የመቀጮው መጠኖች ግን እንደ ተበዳዩና በድለኛው መደቦች ወይም ማዕረጎች ልዩነት ትክክል አልነበሩም። ከሁሉ የተጠበቀው የቤተ ክርስቲያን ነዋይ ነበር፤ ፲፪ እጥፍ ካሣ ነበረበት። እንዲሁም ሁከት በሆነበት ጊዜ ለሰው መሣርያን መስጠት በገንዘብ መቀጮ ተከለከለ።

ይህ ሕግ ፍትሕ የማጫ ሥርዓት እንዲህ ይቀምራል፦

« ስው ሳዱላን በማጫ ቢታጭ፣ (ንብረቱ) እንከን የለሽ ቢሆን የታጩ ይሁኑ። ነውሩ ቢሆን፣ በኋላ ወደ ቤቱ ያምጣው፣ ሰውም በገንዘብ ይስጠው። እርሷ ሕይወት ያለ ልጅ ከወለደች፣ ባልም (ከርስዋ) አስቀድሞ ቢሞት፣ ግማሽ ገንዝብ ትይዝ።... እርስዋ ልጅ ካልወለደች፣ የአባትዋ ቤትሠብ ሀብቱን ጥሎሽንም ይይዙ። ሰው ሳዱላን በወሲብ ቢወስድ፣ ለጠባቂዋ ፶ ሺሊንግ (የወርቅ መሃለቅ) ይካሥ፣ በኋላም የጠባቂዋ ፈቃድ እንደ ሆነ ይታጫት። እርስዋ ለሌላው በገንዘብ የታጨች ብትሆን፣ (ተጨማሪ) ፳ ሺሊንግ ይካሥ። ብትመለስ፣ ፴፭ ሺሊንግ፣ ለንጉሥም ፲፭ ሺሊንግ።»

ዋቢ ድረ ገጽ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]