አስደግፈውት አመለጡ

ከውክፔዲያ

አስደግፈውት አመለጡ

(33)አለቃ መቼም ሲናገሩ ለነገ የለም እና አንዱን ዲያቆን አበሳጭተውት ሊደበድባቸው ይፈልጋቸዋል።እናም አንድ እለት በሩቅ ያዩትና ሮጠው እንደማያመልጡት ሲገባቸው ቶሎ ሮጥ ብለው አንድ ዘመም ወዳለ ጎጆ ይሄዱና ሊወድቅ ያለውን የጎጆውን ግድግዳ በጃቸው ደግፈው እንደቆሙ፤ ዲያቆኑ ይደርስባቸውና ምን እያደረጉ እንደሆነ ይጠይቃቸዋል። እሳቸውም ግድግዳው ሊወድቅ ስለሆነ ደግፈው መቆማቸውን እና እሱ ቢተካላቸው አጣና አምጥተው ግድግዳውን እንደሚያስደግፉ ነግረውት እሱ ሲተካላቸው አለቃ አስደግፈውት አመለጡዋ። አይ የያዛቸው ቀን እኔ የለሁበትም ቆርጦ ቆርጦ ነው የሚጥላቸው