አባል:Nurhussen Gashu
Appearance
በኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ የእስልምና ሚዲያ ተቋማትና ማህበራዊ አገልግሎቶች ላይ በንቃት የሚንቀሳቀስ የሚዲያ ባለሙያ እና ምሁር ነው።

ስለ እርሱ ዋና ዋና መረጃዎች የሚከተሉት ናቸው፡
ግላዊ ታሪክ እና ትምህርት
- የትውልድ ቦታ፦ ቢቸና
- ያደገበት አካባቢ፦ አዲስ አበባ፣ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፣ ሸህ ሆጀሌ (ሸጎሌ) ሰፈር
- የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት፦ በላይ ዘለቀ መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት አዲስ አበባ
- ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት፦ አወሊያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አዲስ አበባ
- ከፍተኛ ትምህርት፦ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስር በሚገኘው ኮተቤ ዲስትሪክት በሒሳብ (Mathematics) የመጀመሪያ ዲግሪ (Bachelor's Degree) ይዟል። በተጨማሪም በሌሎች በተለያዩ ዘርፎች ሰርቲፊኬቶችን ለመያዝ ችሏል። በኤሌክትሮኒክስ፣ ዲጂታል ኤሌክትሮኒክስ፣ ግራፊክስ ዲዛይን፣ ሃላል ፉድ ሰርቲፊኬሽን ...
- ሀይማኖታዊ ትምህርት፦ በኢትዮጵያ እንደ ሸይኽ ኢልያስ አህመድና ኡስታዝ ሙሀመድ አረብ ያሉ የተለያዩ መሻይኾች ስር በመቅራትና እንደ ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር ያዘጋጃቸው ኢስላማዊ ኮትሶችን በመከታተል ሰርቲፊኬቶችን ለማግኘት ችሏል። ቁርአንን ወደ አማረኛ በመመለስ ስራ ላይ ከሚታወቁ መሻይኾች መካከል ታላቁ ሸይኽ ሐጅ በሽር ዳውድ ጋር በህይወታቸው መጨረሻ ላይ በነበራቸው ጥብቅ ቆይታ ከመሞታቸው በፊት ተዝኪያ ሊፅፉለትም ችለዋል።
- ከኢትዮጵያ ውጪ ወደ ኩዌት በመሄድ ኢስላማዊ ኮርሶችን ለመከታተል ችሏል። በቆይታውም ከኩዌታዊው ሸይኽ ኡስማን አል ኸሚስ በቀጥታ ሂቅባ ሚነ ታሪኽ የተሰኘውን የሸይኹን ድርሰት ለመማር ችሏል ሰርተፍኬትም ወስዷል። ወደ ሱዳን በመሄድም ኢስላማዊ ኮርስ በመውሰድ ሰርተፍኬት ለመቀበል ችሏል።
- በአረበኛ ቋንቋ ናህዉን ከሳውዲው ሸይክ ሀሰን ቢን ኸሚስ አልሀማሚ የአጅሩሚያን ኪታብ በመማርና በመሃፈዝ በሰነድ የተያያዘ ኢጃዛ ለማግኘት በቅቷል።

የስራ ልምድ እና አገልግሎት
- ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር፦ ለ7 ዓመታት ያህል በድምፅ ኢዲተርነት ሰርቷል።
- ነሲሓ ቲቪ (Nesiha TV)፦ ለ3 ዓመታት ያህል በድምፅ እና ግራፊክስ ዲዛይነርነት ዘርፍ እንዲሁም የተለያዩ ኢስላማዊ የትርጉም ስራዎችንና የቲቪ ፕሮግራሞችን በመምራት በአገልግሎት ላይ ቆይቷል።
- ሁዳ መልቲሚዲያ (Huda Multimedia)፦ በአሁኑ ወቅት በየዚሁ ኢስላማዊ ሚዲያ ተቋም መስራችና የስራ አባል በመሆን በስራ ላይ ይገኛል።
- በሌሎች ኢስላማዊ እንቅስቃሴዎችም በኢትዮጵያ በተለያዩ ኢስላማዊ ስራዎች ላይ የሚሳተፍ ሲሆን በአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከ/ም/ቤት ስር የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የሚዲያ ዘርፍ ሃላፊ ሲሆን በኢትዮጵያ ሙስሊሞች የጋራ ፎረም ውስጥ የፎረሙ መስራቾች አባል ነው። በአዲስ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ውስጥ የኦዲት እና ኢንስፔክሽን ሰብሳቢ ሲሆን በሌመን ትራቭል የዑምራ ዘርፍ ላይም ሃላፍትና ወስዶ የኡምራ ስራ ላይ በመሳተፍ ይታወቃል።