አባታችን ሆይ

ከውክፔዲያ

አባታችን ሆይ (ግዕዝአቡነ ዘበሰማያት) ወይም የጌታ ጸሎትማቴዎስ ወንጌል 6 እና በሉቃስ ወንጌል 11 ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ያስተማረው ጸሎት ነው። ጸሎት የግል መሆኑን ካስረዳ በኋላ፥ ጸሎት ግን በገሃድ ስትፈልጉ፥ እግዜር የምትፈልጉትን ገና ስላወቀ፥ እንዲህ ብላችሁ ጸለዩ በማለት አስተማራቸው። በማቴዎስ ወንጌል 6፦

በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ፣ ስምህ ይቀደስ፤ መንግሥትህ ትምጣ፣ ፈቃድህ በሰማይ እንደ ሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን፤ የዕለት እንጀራችንን ዛሬ ስጠን፤ እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን፣ ከክፉም አድነን እንጂ ወደ ፈተና አታግባን፤ መንግሥት ያንተ ናትና ኃይልም ክብርም ለዘለዓለሙ አሜን።

ሉቃስ ወንጌል 11 ከማቴዎስ ትንሽ ይለያል፦

በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ፣ ስምህ ይቀደስ፤ መንግሥትህ ትምጣ፣ ፈቃድህ በሰማይ እንደ ሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን፤ የዕለት እንጀራችንን ዕለት ዕለት ስጠን፤ ኃጢአታችንንም ይቅር በለን፣ እኛ ደግሞ የበደሉንን ሁሉ ይቅር ብለናልና፣ ከክፉም አድነን እንጂ ወደ ፈተና አታግባን።

በአብያተ ክርስቲያናት በጋራ በአማርኛ ሲጸለይ ከጥቃቅን ልዩነቶች ጋራ እንዲህ ነው፦

አባታችን ሆይ! በሰማያት የምትኖር
ስምህ ይቀደስ መንግስትህ ትምጣ
ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁም በምድር ትሁን
የዕለት እንጀራችንን ስጠን ለዛሬ
በደላችንንም ይቅር በለን
እኛም የበደሉንን ይቅር እንደምንል
አቤቱ ወደ ፈተና አታግባን
ከክፉ ሁሉ አድነን እንጂ
መንግሥት ያንተ ናትና
ኅይል ክብር ምስጋና ለዘለዓለሙ
አሜን!

አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ፣ ትምጻእ መንግሥትከ ፣ወይኩን ፈቃድከ ፣ በከመ በሰማይ ፣ከማሁ በምድር፣ ሲሳየነ፣ዘለለ ዕለትነ፣ሃበነ ዮም። ኅድግ ለነ፣አበሳነ ወጌጋየነ፣ ከመ ንሕነኒ ንኅድግ ለዘአበሰ ለነ። ኢታብአነ እግዚኦ ውስተ መንሱት፣ ኣላ አድኅነነ ወባልሐነ፣እምኩሉ እኩይ፣ እስመ ዚኣከ፣ይእቲ መንግሥት፣ኃይል ወስብሐት፣ ለዓለመ ዓለም፣አሜን።


በሰላመ፣ ቅዱስ ገብርኤል መልአክ፣ ኦ እግዝእትየ ማርያም ሰላም ለኪ፣

ድንግል ብኅሊናኪ ፣ወድንግል በሥጋኪ።

እመ እግዚአብሔር ጸባዖት ሰላም ለኪ። ቡርክት አንቲ እምአንስት፣ ወቡሩክ ፍሬ ከርሥኪ። ተፈሥሒ ፍሥሕት ኦ ምልእተ ጸጋ እግዚአብሔር ምስሌኪ። ሰአሊ ወጸልዪ ምሕረት በእንቲኣነ፣ ኀበ ፍቁር ወልድኪ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ከመ ይሥረይ ለነ ኃጣውኢነ።

በአማርኛ

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ ፥ በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል ሰላምታ ሰላም እልሻለሁ። በሀሳብሽ ድንግል ነሽ ፤ በሥጋሽም ድንግል ነሽ አሸናፊ የእግዚአብሔር እናት ሆይ ሰላምታ ላንቺ ይገባሻል ከሴቶች ሁሉ ተለይተሽ አንቺ የተባረክሽ ነሽ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው። ጸጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ ልዑል እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ነውና ከተወደደው ልጅሽ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ይቅርታንና ምሕረትን ለምኝልን ኃጢአታችንን ይቅር ይለን ዘነድ ለዘለዓለሙ አሜን። (የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ ፩ ፥ ፳፮ - ፶፰።)

የእግዚአብሔር አብ ጸጋ ፣ የእግዚአብሔር ወልድ ቸርነት ፣ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አንድነት ከሁላችን ጋር ይሁን ለዘለዓለሙ አሜን። (፪ኛ ጢሞቴዎስ ምዕ ፩ ቁ ፪።)