አባይ በለጠ

ከውክፔዲያ

አባይ በለጠ ታዋቂ ኢትዮጵያዊ ድምፃዊ የነበረ ሲሆን ለስላሳ ወይም የትካዜ ዜማዎች በመጫወት ይታወቃል።[1]

የህይወት ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

አባይ በለጠ በ፲፱፻፶፬ ዓ.ም. አሪዞና የምሽት ክበብ ውስት በድምፃዊነት ተቀጥሮ ድምፁን ከሙዚቃ ጋር ሲያርቅ ከቆየ በኋላ በዚያው ዓመት በጦር ሠራዊት ክፍል በድምጻዊነት ተቀጥሮ ለ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. መግቢያ እንቁጣጣሽ በዓል በመድረክ ላይ ወጥቶ በሕዝብ ፊት መጫወት ጀመረ። ሙዚቃን እንዲወድ በይበልጥ ስሜት ያደረበት እራሱ መጫወት ከጀመረ በኋላ እንደሆነ አባይ ይናገራል።[1]

የሥራዎች ዝርዝር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

እስከ ፲፱፻፶፯ ዓ.ም. ድረስ ፲፫ ያህል ዜማዎችን ተጫውቷል። ከእነርሱም መካከል «የአዲስ አበባ ውበት»፣ «ምነው ብታስቢ» እና «ሳገኝ ከተፍ ያለች» የሚባሉት ይገኙበታል።[1]

ማጣቀሻ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ "ናሽናል ቢብሊዮግራፊ ቡድን፣ የአንጋፋ አርቲስቶች መዝገበ የሕይወት ታሪክ፣ መጋቢት ፳፻፣ ገጽ 31". Archived from the original on 2011-09-29. በ2010-12-18 የተወሰደ.