አጭር የአማራ ማታገያ ሀሳብ

ከውክፔዲያ


ከሁሉም ማስተዋል ይቅደም

በ1960ዎቹ የስልጣን ጥመኝነት ጥላቻ የቅኝ ገዥ ፍላጎት አስፈፃሚ የኢትዮጵያን የወቅቱን የፖለቲካ አሰላለፍ ያልተረዱ የተዘበራረቀ የፖለቲካ አላማ ያላቸው እና በስሜት ያበዱ እንደነ ኦነግ ሕዋሓት መኢሶን  እና ኢህአፓ የመሳሰሉት  የፖለቲካ ሀይሎች የነበሩበት ወቅት ነዉ፡፡ የገባዉም ያልገባዉም የመገንጠል ፍላጎት ያለዉም የሌለዉም ከዉጭ ጠላት የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግለትም የማይደረግለትም  በአንድ ላይ ጃንሆይ ላይ ተነሱ፡፡ ግራ የገባቸው ቅኑ ንጉስ ማስተዳደር ከቻላችሁ ዙፋኑ ይሄው ብለው ስልጣናቸውን ለቀቁ፡፡ አለቀ!!! የመንጋ ፖለቲካ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ኢትዮጵያን ሽባ አደረጋት!!! ንጉሱ ከስልጣን ወረዱ!!! የስልጣን ጥመኛ የሆነ ሀይል በያዘው አፈሙዝ እነ መኢሶንን እያሰፈራራ ስልጣን ላይ ቁብ አለ፡፡ ዲፕሎማቶች ሚኒስተሮች እና የጦር ጀኔራሎች ተረሸኑ፡፡ ይሄዉ የፖለቲካ ብስለት የሌለዉ ሀይል የኢትዮጵያን እንቁ ልጆች መቁረጥ ጀመረ፡፡ መንጋዉም ተፀፀተ እንደገና ደርግን አወገዘ ግን አሁንም መንገዉ ላይ የጥይት ናዳ ወረደ፡፡ ከዚህ ላይ ብዙ ትዉልድ አለቀ፡፡  ይህን ሁሉ የወለደው አለማስተዋል እና ሰሜት ያነገበ የመንጋ ፖለቲካ ነው፡፡  ሁሉም ከንጉሱ በኋላ የተሻለ መንግስት መጥቶ የተሻለ ሂወት የሚቀጥል መስሎት ነበር፡፡ ነበር ነው፤ ግን አልሆነም፡፡ ከአፄ ሐይለ ሥላሴ በኋላ ሀገር የሚያስተዳደር ብቁ ሀይል አልነበረም፡፡ ሁሉም ሀገሪቱ እና ህዝቡ በማያውቁት የሶሻሊዝም  የፖለቲካ መጠጥ  ሰክሯል የሀገሩን ፖለቲካ መረዳት ከብዶታል፡፡ደርጉ ደግሞ መልክህ አላማረኝም በማለት የሰከረዉንም ያልሰከረውንም ይረሽናል፡፡ ከጥይት ቀላ የተረፈው ትዉልድ የደርጉ ደካማ ያገር ዉስጥ እና የሀገር ዉጭ ፖለቲካ ለፈጠረው እሳት ማገዶ ሆነ፡፡   በመጨረሻም ባልተጠበቀ መንገድ የፖለቲካ ብስለት የሌለዉ ወታደራዊ ሀይል ህዝቡን እንዳሰቃየ ሕዋሓት በሚባል ሌላ የኢምፐሪያሎች ባሪያ የሆነ ባንዳ የፖለቲካ ስርዓት ተተካ፡፡ የሀገሪቱ  እና የህዝብም ስቃይ ለ 27 ዓመታት ቀጠለ፡፡ በተለይ ይህ ማፊያ የፖለቲካ ድርጅት አማራ-ጥል ማኒፌስቶ እና ህገ-መንግስት ከማዘጋጀት እስከ አማራ የዘር ጭፍጨፋ የደረሰ ኢ-ህጋዊ ኢ-ሰባዊ እና ኢ-ሞራላዊ ስራ በመስራት የነጭ አለቆችን አስደሰተ፡፡ ኋላም ቁጭት በወለደው መራር የአማራ ትግል ለመቀበር በቃ!!! በመጨረሻም እኔም የዉስጥ ትግል አደርጌአለሁ የሚል ከዚያው ከህዋሓት የወጣ ግን በህዋሓት አስተምሮ ያደገ በምስራቅ አፍሪቃ ሉአላዊ የሆነች ኦሮሚያ የምትባል ሀገር በአጭር ጊዜ መመስረት ያሰበ የካቢኔ ስብስብ ብልፅግና በሚል ስያሜ ስልጣኑን ያዘ፣ ስልጣኑን በያዘ ንጋት ከፍተኛ ድጋፍ ያገኘዉ ከአማራ ህዝብ በኩል ነበር፤ ግን በማግስቱ አማራ የለመደውን ሞት ባለመደው ሰይጣን መጎንጨት ጀመረ! የአማራ ስቃይ መቆም አልቻለም! ጭራሽ የዚህ የፖለቲካ አመራሮች አማራ ጠሎችን በማሰባሰብ በአደባባይ አማራ ላይ የዘር ፍጅት አውጀው አማራዉን ማሰገደል ቀጠሉ….. ወዳጀ  በ1960ዎቹ  የተፈጠረች አለማስተዋል ይህን ሁሉ መከራ ወለደች!!! እስቲ እያስታዋልን!!

1.    መግቢያ

ወደ ዋናዉ ፅሁፍ ከመግባታችን በፊት በወፍ በረር የ አምሓራ ምንነትን ከስረወቃላዊ ነገዳዊ እና ብሄራዊ ትንታኔ ጋር አያይዘን እንመለከታለን፡፡ ከስረወ-ቃል አኳያ አምሓራ ማን ነዉ የሚለዉን በተመለከተ የአለቃ ታየ ገብረ-ማሪያምን አና የአቶ አጽሜን ሀሰብ ጨምቆ መመልከቱ ጥሩ ነዉ፡፡፡ሙህራኑ አምሓራ  የሚለዉ ቃል ከእብራይስጥ ሂሜያርት ከሚባል  ቃል እና ከግዝ አም-ሓራ ከሚባል ቃል ሊመጣ እንደሚችል ግምታቸዉን ከአስቀምጡ በኋላ አምሓራ  የሚለዉን ቃል   ጨዋ ሀያል ህዝብ እና ነፃ ህዝብ በማለት  ይተነትኑታል(ታየ፣1898)፡፡  ዓስራት(2008) የአለቃ ታየን የኢትዮጵያ ህዝብ ታሪክ መፅሀፍ እና የመራሪስ አማንን መፅሀፈ ኢብርሐት  አጣቅሶ እንደፃፈዉ  የአምሓራ ነገዳዊ የዘር ግንደ ከሴም ግንድ ከሆነው አርፋክሳድ የሚመዘዝ ነዉ፡፡ አምሓራ ሴማዊ ህዝብ ነዉ፡፡

ሌላዉ የአምሓራ የብሄር ማንነት ጉዳይ ነዉ፡፡ አዲስ አበባ ዪኒቨርሰቲ(2006) የአማራኛ መዝገበ ቃላት በሚል ርዕስ ባሳተመዉ መፅሀፉ ብሄርን አንድ አይነት ባህል እና ስነ-ልቦናዊ አመለካከት ያለዉ በታሪክ እና በኢኮኖሚ የተሳሰረ ህዝብ በማለት  ይገልፀዋል፡፡ አንቶኒ ሰሚዝ የሚባል ሙህር በ2001 እ.ኤ.አ በፃፈዉ የብሄር ማንነት አተረጓጎም በሚለዉ መፅሀፉ ብሄር ማለት በባህል እሳቤ  በትዉስታ በቋንቋ  በዘር ግንድ እና በታሪክ አንድ የሆነ የማህበረሰብ ስብስብ  ነዉ ይላል፡፡፡ አምሓራ ከላይ በተጠቀሱት የብሄር ትርጓሜ  ሚዛን ሲታይ ብሄር ነዉ፡፡ በሁሉም አቅጣጫ የሚኖር አምሓራ ተመሳሳይ ባህል አለዉ አንድ የሚያደረገዉም የታሪክ ገድል አለዉ፤ ተመሳሳይ ስነልቦናዊ ስሪትም አለዉ፤ ከዚህም በተጨማሪ የራሱ  የዘር ግንድ አለዉ!!!!

ሁኖም አንዳንድ በበታችነት ስሜት የተጠቁ በአምሓራ መሰዋት ኢትዮጵያን ማቆየት የሚሹ እንዲሁም  ሌሎች ትናንሽ ሉአላዊ ሀገራትን መፍጠር የሚፈለጉ የኢምፐሪያሊስት ባሪያዎች የ1960  ፀረ- አምሓራ ሙህራን ፀረ-አምሓራ-ኢትዮጵያዊ ፖለቲከኞች እና ድንዙዝ ተከታዮቻቸዉ አምሓራን ከሀይማኖት  ከቋንቋ እና ከኢትዮጵያዊነት ጋር በማላተም እንዲሁም የአምሓራ መኖሪያ የሆኑ የወሎ የሽዋ የጎጃም እና የጎንደር ክፍለ-ሀገራትን እንደማንነት በመቁጠር አምሓራ  የሚባል ማንነት የለም ይላሉ፡፡ ፀረ- አምሓራ ሙህራኖች አምሓራን በስሜን ኢትዮጵያ ብቻ በተለያዩ አከባቢወች የሚኖር የአማረኛ ቋንቋ ተናጋሪ እና የኦርቶዶክስ ሀይመኖት ተከታይ የሆነ ማህበረሰብ ይሉታል(ዓስራት፣2008 እና ይሁኔ፣2010)፡፡ፀረ-አፍሪቃ ፀረ-ኢትዮጵያ እና  አውሮፓ አፍቃሪ ፖለቲከኞች  የግል ጥቅማቸዉን ለማስጠበቅ ስልጣን ለመያዝ የኢትዮጵያን ሀብት ለመመንዘር እና ኢትዮጵያን ለማፍረስ ኢትዮጵያን እየጠበቀ ያለዉን አምሓራ ማዳከም ስላለባቸዉ አምሓራ ጨቆኝ ሌላዉ ተጨቋኝ ነበር የሚል ትርከት ፈጥረዉ ይታያሉ(ግርማ፣2008)፡፡

ይህ ለዘመናት የቆየ ኢ-ተገቢያዊ  ፀረ-አምሓራ እና ፀረ-ኢትዮጵያ ሴራ በአንድ በኩል  አምሓራ ግላዊ ባህሪ አንዲያዳብር እና በህልዉናዉ ላይ የተጋረጠበትን አደጋ እንደ ብሄር አንድ ሁኖ እንዳይመክት ትልቅ እንቅፋት ሁኖ ይገኛል፡፡ በሌላ በኩል በኢትዮጵያ የተለያየ ክፍል ያሉ ብሄሮች አምሓራን ጠላት እና ገፊ አድረገዉ አምሓራዉ ላይ እሰር እና ግድያ እእዲፈጽሙ መንገድ የከፈተ ነዉ፡፡ ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮሀል(A whip makes a jittery cry after flogging) እንደሚባለዉ ከአስራ ስድስተኛዉ ክፍለ ዘመን ጀምሮ  አምሓራ በኦሮሞ እና በአዳል ሱልጣኖች መሳደዱ ሳያንሰዉ፤ እንዲሁም ለባለፉት አመታት በአባገነናዊ የደርግ ስርዓት እንዲሁም በትህነግ አስተዳደር የደረሰበት የግፍ ጠባሳ ገና ሳይደርቅ ጭራሽ በግልባጭ ለባለፉት ችግሮች ሁሉ አምሃራ ተጠያቂ ሁኗል፡፡ ስለዚህ አምሓራዉ አንድነቱን አጠነክሮ እና ህለዉናዉን አረጋግጦ  እራሱን ያድን ዘንድ እና ኢትዮጵያን ያቆይ ዘንድ የአምሓራ መደራጀት ብሄርተኝነት እና ህልዉናን የማቆየት አስፈላጊነት ላይ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ ነዉ፡፡

'