ኢርካብ-ዳሙ

ከውክፔዲያ
የኤብላና የማሪ ግዛቶች፣ 2109 ዓክልበ. ግድም

ኢርካብ-ዳሙ ከ2115-2109 ዓክልበ. ግድም የኤብላ ንጉሥ ነበር። የኤብላ ጽላቶች የተባሉት ሰነዶች ክምችት ይህን ዘመን ይጠቅላል። የማሪ ንጉሥ ኢብሉል-ኢል ከኤብላ ብዙ መሬት በጦርነት ይዞ ነበር። በኢርካብ-ዳሙ መጀመርያው ዓመት ግን የኤብላ ሻለቃ ኤና-ዳጋን ኢብሉል-ኢልን አሸንፎ አዲስ ንጉሥ ኒዚ በማሪ ዙፋን አነሣ። በቅርብ ጊዜ ግን ኤና-ዳጋን እራሱ የማሪን ንጉሥነት ማዕረግ ያዘ።

ኢርካብ-ዳሙ ደግሞ ከሐማዚ ንጉሥ ዚዚ ጋራ ስምምነት እንደ ተዋዋለ ይዘገባል።

ቀዳሚው
ኢግሪሽ-ሐላብ
ኤብላ ንጉሥ
2115-2109 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
ኢሻር-ዳሙ