ኩሩቭ

ከውክፔዲያ
የኩሩቭ አርማ

ኩሩቭ (Kurów) በደቡብ-ምሥራቅ ፖሎኝ ያለች መንደር ናት። ከፑዋቪ እና ከሉብሊን ከተሞች መካከል በኩሩፍካ ወንዝ ላይ ትገኛለች። በ1997 2,811 ኗሪዎች ነበሩባት።

ጳጉሜ 4 ቀን 1931 ዓ.ም. መንደሪቱ በጀርመን ሉፍትቫፈ (የአየር ኀይል) በቦምብ በጣም ተደበደበች። በጦርነቱ ጊዜ ጀርመኖች የባርዮች ሠፈር እንድትሆን አደረጉዋት። ዳሩ ግን አብዛኛው የታሠሩት ፖሎኞች ወደ ጫካ አምልጠው አርበኞች ሆኑ።