ክርስቲያኖ ሮናልዶ

ከውክፔዲያ
ክርስቲያኖ ሮናልዶ 2022 ዓም

የክርስቲያኖ ሮናልዶ ዶሳንቶስ አቪየሮ «1985-» ሰፊ የህይወት ታሪክ (ክፍል አንድ)

20/11/2017  ብርሃን ስፖርት

በፕላኔታችን ኳስን በላቀ ደረጃ ከሚጫወቱ ሁለት ተጨዋቾች አንዱ ፤እንደ አጥቂም እንደ ክንፍ ተጨዋችም ቢጫወት ጎል እንዳሻው የሚያገባ፤ኳስ ከፍጥነቱ ሳይደናቀፍ የሚያንከባልል ጨራሽ የፍፁም ቅጣት ምት ስፔሻሊስት፤አንድ ለአንድ ማንኛውንም ተከላካይ የሚያሸብር …….​

ይህ የዛሬ ኮከብ የሴት ቅድመ አያቱ ኤልዛቤል ዳፒዳድ በአፍሪካዊቷ ሃገር ኬፕ ቨርዴ የተወለዱ ናቸው፤ከአንድ ወንድሙ እና ከሁለት እህቶቹ ጋር በአንዲት ክፍል ውስጥ ኑሮን ለማሸነፍ እንደተጋ የልጅነት ታሪኩ ያስረዳል፤ታዲያ በአንድ ወቅት ይህንን ህይወታቸውን በእግር ኳስ ብቻ ለመቀየር ከእናቱ ጋር ይስማማል፤ለዚህም የሃገሩን ክለብ ስፖርቲንግ ሊዝበን ይቀላቀላል፡፡ በ15 አመቱ ግን እግርኳስን እንዲያቆም የሚያስገድድ የልብ ህመም እንዳለበት ይታወቃል፤በእናቱ ስምምነት መሰረት ቀዶ ጥገና ተደርጎለት ወደ እግር ኳስ ይመለሳል፡፡​

ስፖርቲንግ ሊዝበን እያለ በ2002 ከአርሰን ቬንገር ጋር ተገናኝቷል ወደ ሊቨርፑል የመሄድ እድልም ነበረው፡፡ በመሃል ግን ሰር አሌክስ ፈርጉሰን እና ዩናይትድ ትኩረት ውስጥ ገባ፤በ2003 ስፖርቲንግ ሊዝበን ማንቸስተር ዩናይትድን በወዳጅነት ጨዋታ 3ለ1 አሸነፈ፤ያኔ የማንችስተር ተጨዋቾች ወሬ ሁሉ ስለ ሮናልዶ ሆነ ወዲያውኑ ይሄ ልጅ ወደ ማንቸስተር ዩናይትድ እንዲመጣ ሰር አሌክስ ፈርጉሰንን መወትወት ጀመሩ፡፡​

በ2003-04 የውድድር ዘመን በ£12.4m ሮናልዶ ቀያይ ሰይጣኖቹን ተቀላቀለ ፤እነ ጆርጅ ቤስት፣ብሪያን ሮብሰን፣ኤሪክ ካንቶና ዴቪድ ቤካም የለበሱትን 7ቁጥር መለያ ለበሰ፤ባለተሰጥኦው ተጨዋች የማንቸስተርን ውድ ቁጥር ፈርጉሰን መረጡለት፤የክርስቲያኖ ሮናልዶ ተአምር ገና በመጀመሪያው ጨዋታ ከቦልተን ወንደረርስ ጋር ታየ፤አዲስ የእግር ኳስ ሰው መወለዱ እውን ሆነ፤ከሁለት የውድድር አመታት በኃላ ደግሞ ክርስቲያኖ ሮናልድ የኦልድትራፎርድ ቁንጮ ተጨዋች ሆነ፡፡

በ2006-07 የውድድር ዘመን ከ20 በላይ ጎሎችን አስቆጠረ ፤በሊጉም በ2008 ከዩናይትድ ጋር ፕሪሚየር ሊጉን እና የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግን አነሳ፤በዚህ የውድድር ዘመን በሁሉም ውድድሮች 42 ጎሎችን በማስቆጠር ምርጥ ተጨዋችነቱን አስመሰከረ ፤በ2008 በዩናይትድ ባሳየው ምርጥ እንቅስቃሴ የተነሳ ክርስቲያኖ ሮናልዶ ለመጀመሪያ ጊዜ የባሎንዶር ሽልማትን አገኘ፡፡

ያኔ ኮከብ የሚያሳድዱት ማድሪዶች የኦልድ ትራፎርድን በር ማንኳኳት ጀመሩ፤ሮናልዶ ከኦልድትራፎርድ ይለቃል እየተባለም ግን ማን ዩናይትድ በዚህ ጥበበኛ ፖርቹጋላዊ ጎል አምራችነት ለተከታታይ 3አመታት የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ አነሳ(ከ2007-09)፡፡በ2009 ዩናይትድ እንደገና ከባርሴሎና ጋር ለሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ ደረሰ፤ባርሰሎና በዚህ ጨዋታ 2ለ0 አሸነፈ፤ያ ጨዋታ ሮናልዶ የዩናይትድን ማሊያ የለበሰበት የመጨረሻው ትልቅ ጨዋታ ሆነ፡፡​

ከሳምንታት በኃላ የዝውውር ሪከርድ በጥበበኛው ኮከብ ተሰበረ፡፡ማድሪድ £80m ከፈለ፤ሮናልዶ የልጅነት ህልሜ ወዳለው ሳንቲያጎ ቤርናቦ ተዘዋወረ፤አዲሱ ተፅዕኖ ፈጣሪ ታታሪው ጋላክቲኮን ተቀላቀለ፡፡በሳንቲያጎ ቤርናቦ በመጀመሪያው አመት ብቻ በ35 ጨዋታዎች 32ግቦችን አስቆጠረ ፤በ2010-11 የውድድር ዘመን ደግሞ የላሊጋው ኮከብ ግብ አስቆጣሪ ሆኖ የፒቺቺው አሸናፊ ሆነ፤በ34 ጨዋታዎች 40ግቦችን በማስቆጠር፤ሪያል ማድሪድ ባርሰሎና በኮፓ ዴል ሬይ በዚህ ዘመን ሲያሸንፍ የማሸነፊያ ጎሏ የክርስቲያኖ ሮናልዶ ሆነች፡፡

በሪያል ማድሪድ ሮናልዶ መነሳቱን አላቆመም በየጊዜው የሚጨምር የማይታመን ብቃት የሚያሳይ የጎል ማሽን ሆነ፤በ2012 ላሊጋውን ከማድሪድ ጋር ወሰደ፤በ38 ጨዋታዎች 46 ጎል በማስቆጠር ኮከብ ሆነ በዚህ ወቅት የፊፋ ባሎንዶርን ሌላ ልዩ ብቃት ባሳየው አርጀንቲናዊው ሊዮኔል ሜሲ ተነጠቀ እንጂ ሮናልዶ መሸለም ነበረበት ብለው የሚከራከሩት በርካታ ናቸው። ሮናልዶ እስከ አሥር አመቱ ሀልጋ ላይ በመሽናቱ እናቱን ያስቸግር ነበር እናቱ ደይፐር መቀየሪያ እንኳን አልነበራትም አሁን ጎብዞ የአለም ሪከርድ እየሠራ ይገኛል ስለሱ ታሪክ ተፅፎ አያልቅም።በአሁኑ ወቅት አርናስል ውስጥ ይገኛል።