ውይይት:ቅኔ

Page contents not supported in other languages.
ከውክፔዲያ

196.29.61.86[ኮድ አርም]

የሄዋን ልጅ እንስት ሂጅ አላልኳት እኔ ልሄድ ነው ብትለኝ አይኔን ከፈት ከደን ማመን እስኪያቅተኝ አስጀምራኝ ፍቅርን ባንድ ነን ዘላለም ሀ ብዬ ቀረሁኝ ሁን እንኳን ሳልደግም ይዛኝ ወጥታ ራሷ ፍቅር እዚ አለ ብላ ትታኝ እልም ብትል ብቻዬን ባውላላ ሜዳ ላይ ያለ አጋር ብቻዬን ስዋትት ቀና ብለው ሰማይ ባጎነብስ መሬት [/u]አክስመሽው ልቤን የመገበሽ ፍቅርን አልፎ እንደው ላይተወኝ ጎሽሞት ጎኔን ቢሄድ ካይኔ ርቆ ፍቅርሽ ከእይታ ያመሰገንኩሽን እንዳልረግምሽ ላፍታ ጠልቼሽ ለጠዪ ጨክኜ እንዳልሰጥሽ ትዝ ሲለኝ ድንገት የሄዋን ልጅ እንስት ሴት ልጅ መሆንሽ መብከንከኔን ከዳር ጣል አደርገውና ይሁና እላለው እስኪ እንደው ይሁና የሄዋን ልጅ እንስት መሆንሽን አምኜ ትተሽን ስትሄጂ ብቀር ለብቻዬ ፍቅሬን እንዳታዪው ምኞት ቢያሳውርሽ አካልሽ ከኔ ጋር ሄዶ ከዚያ ልብሽ እጄን ባፌ ጭኜ ቢገርመኝም ቅሉ የሄዋን ልጅ እንስት ነች 'ኮ እያሉ ሲነግሩኝ እነሱ ያወቁትን ድሮ ግዜያቶችን ወስዶ ደርሶ ከኔ ጆሮ ሲናጥ ጭንቅላቴ ወደላይ ወደታች ተከፍቶ ላንቃዬ አይኔ ሲቁለጨለጭ ልቤ ሲመታብኝ ቢገባኝ ነገሩ አልመልስ ውሎዬን አልሆነም አዳሩ እና እኔ ልመለስ ከሄደ 'ጋ አይኬድ ጎዳናው ሌላ ነው የያዘችው መንገድ በውጋም የዛኔ በፍቅር አውድማ ላይ ቁስሌ ቢበረታም ስቃዬ እኔን ቢያጋይ ብትጨክኚም በኔ ብትጥይኝ ከመሬት ምንስ ይደረጋል የሄዋን ልጅ እንስት ነሽና የኔ እህት አይግረመው ልቤ አዲስ ነገር የለም የነበረ ያኔ ይቅር ብዬሻለው ይቅር ይሁንሽ ይሳካ ይመር መንገዱ ይቅናልሽ እንጂ እኔማ አንቺን አልጠላሽም በውነት መች መሆንሽ ቀረ የሄዋን ልጅ እንስት