ዛጔ ሥርወ-መንግሥት

ከውክፔዲያ

የአማራ ሥርወ-መንግሥት እና ነገድ በኢትዮጵያ

አማራ ማለት በቋንቋው አማርኛ እና ግዕዝ ሲኾን ትርጉሙም ነጻ ህዝብ ማለት ነው፡፡ የአማራ ሥርወ መንግሥት እና ነገድ በጥንታዊት ኢትዮጵያ ከአክሱም መንግስት በፊት የዳማት ስርዎ መንግስት አንስቶ እስከ 1975 አ ም በኢትዮጵያን በመንገሥ ለተከታታይ ከ3000 ዓመታት በላይ አስተዳድሯል፡፡ ከታወቁ ታላላቅ የአማራ ነገስታት መካከል (ቅዱስና ንጉሥ) በመኾን በተከታታይ የነገሡት አራት ቅዱሳን፡

           ፩) ቅዱስ ይምርሐነ ክርስቶስ

           ፪) ቅዱስ ሐርቤ (ገብረ ማረያም)

           ፫) ቅዱስ ላሊበላ

           ፬) ቅዱስ ነአኩቶ ለአብ    ናቸው፡፡

እነዚህ ነገሥታት ዕድሜ ዘመናቸውን ሙሉ ሀገራቸው ኢትዮጵያን በሃይማኖታዊ፤ ማኅበራዊ፤ ትምህርታዊ እና ኢኮኖሚያዊ  ልማት ከፍተኛ ጥረት ያደረጉ ናቸው፡፡ በሀገራችን ታዋቂ የቱሪስት መስህብ ከሆኑት ቅርሶች መካከል የታላቁ የላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናትን የገነቡት እነዚህ ታላላቅ ቅዱሳን ነገሥታት ናቸው፡፡ እነዚህ አብያተ-ክርስቲያናት የተሰሩት ከአንድወጥ ትልቅ ዐለት ላይ መሆኑ ዓለምን ያስደነቀ ቅርስ ነው፡፡ ስለእነዚህና ሌሎችም ነገሥታት ታሪክና ሥራ ቀጥሎ በስፋት እናቀርባለን፡፡    

የአማራ ነገድ እና ታሪክ

አገው ልቡ ዘጠኝ ስምንቱን አኑሮ በአንዱ አጫወተኝ የተባለበት ታሪክና ምክንያት አለው፡፡

አማራ ማለት እንደ እግዚአብሔር ልበ ሰፊ ነገር አላፊ ነው ማለት ነው፡፡ ወልደ እግዚአብሔር መድኀኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ደግሞ (ኩኑ ጠቢባነ ከመ እባብ ወየዋህ ከመ አርዌ ርግብ) እንደ እባብ ልባሞች አንደ ርግብ የዋሆች ኹኑ ፤ ብሎ አዝዞናል እንጂ ከአህዛብ እና ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ ሂዱ ኑሩ ተደባለቁ አላለንም፡፡

       ምንጭ፡ (የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከልደተ ክርስቶስ እስከ 2000 ዓ.ም ገፅ-136)

አባ አውግስጢኖስም ይህንን የክርስትና ሕይወት በአጽንኦት ሲገልጹትና ሲመክሩን በክርስትና ህይወት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የምድር ጨው እና የዓለም ብርሐን ሆኖ በሃይማኖትና ምግባር መኖር ነው እንጂ በአሕዛብ ማኅብራዊ ጣጣ ውስጥ ገብተን መደባለቅ የለብንም ብለዋል፡፡        

ከታሪክ ስንነሳ የአገው ህዝብ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሐይማኖቱ ጠንካራ አማኝ ና በሐይማኖት ጉዳዮች ላይ በፅናት በመቆም ሚስጥራትን የሚጠብቅ ነው፡፡ በሐይማኖት ጉዳዮች ላይ ቀልድና ዋዛ ፈዛዛ አይወድም፡፡ ከእንግዳ ሰዎች ወይም ከባዕድ ጋር ሲገናኝ ደግሞ በቶሎ ተግናኝቶ አይመሳሰልም ፤ አይደባለቅም ፡፡ ነገር ግን እንግዳውን በአግባቡ እያስተናገደ በልቡ ግን ይመረምረዋል፡ ያጠናዋል፡ የምን እምነት ተከታይ እንደሆነ ፤ ኑሮው አና ባህሉ አንዴት እንደሆነ ለማዎቅና ለመጠንቀቅ ይሞክራል፡፡ ወዲያውም እውነተኛ አማኝና ክርስቲያን መሆኑን ሲያረጋግጥ እንደ ርግብ የዋህ ይሆንለታል ማለት ነው፡

የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በዘመነ ዛጉዌ ሥርወ-መንግስት

ዛጔ የሚለዉ ስያሜ የሥርወ-መንግሥቱ ተዋናዮች (Actors) የነገደ አገው ተወላጆች ስለኾኑ የአገው መንግሥት ለማለት ’’ዘአገው’’ ከሚለው ቃል የተወሰደ ነው፡፡ ለዛጔ ሥርወ መንግሥት ነገሥታት የዘር ግንድ መሰረት የኾነው መራ ተክለሃይማኖት የአክሱም መንግሥት ካከተመ በኋላ በትረ መንግሥቱን ጨብጦ መናገሻ ከተማዉን ወደ ላስታ በማዛወር በኢትዮጵያ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ እነዲጀመር ምክንያት ኾኗል፡፡ ከመራ ተክለሃይማኖት ዠምሮ ከሦስት መቶ ዓመታት በላይ ዐሥራ አንድ የዛጔ ነገሥታት ኢትዮጲያን እንደ አስተዳደሩ ትውፊታዊ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ከነዚህም መካል አራቱ ክህነትን ከንግሥና ጋር አስተባብረው የያዙ እና በቤተክርስቲያን ቅድስናቸዉ የሚታወቁ ናቸው፡፡

ካህናት ነገሥታት የሚባሉት

ከአስራአንዱ የዛጔ ሥርወ-መንግሥት ነገሥታት መካከል ቀደም ብለን እንደገለፅናቸው፣  ካህናት ነገሥታት በመባል የሚታወቁት አራት ናቸው፡

           ፩) ቅዱስ ይምርሐነ ክርስቶስ

           ፪) ቅዱስ ሐርቤ(ገብረ ማረያም)

           ፫) ቅዱስ ላሊበላ

           ፬) ቅዱስ ነአኩቶ ለአብ ናቸው፡፡

እነዚህ ነገሥታት ለክርስትና እምነታቸዉ የነበራቸዉ ፍቅር፣ያደረጉት መስዋዕትነትና ውለታ ማንነታቸዉን ይገልፃቸዋል፡፡ በርግጥ ኹሉም የዛጔ ነገሥታት ክርስቲያኖች ስለነበሩ በዮዲት ጉዲት የጥፋት ዘመቻ ምክንያት፡

-ተመናምኖ የነበረዉን ክርስትና እንደገና እንዲያንሠራራ ማድረጋቸው

-ተስፋ የቆረጠዉን ሕዝበ-ክርስቲያን እንዲፅናና፣ማድረጋቸው

-የተቃጠሉ መጽሐፍት እንደገና እንዲፃፉና ማድረጋቸው እና

-የፈረሱ አብያተ ክርስቲያናት እንደገና እንዲሰሩ ያደረጉት ጥረት፤

በኢትዮጲያ ቤተክርስቲያን ታሪክ የሚረሳ አይደለም፡፡ ከሁሉም በበለጠ እነዚህ አራቱ ነገሥታት ሙሉ ሕይወታቸውን ለመንፈሳዊ ነገር አዉለዉ አብያተ ክርስቲያናትን በማነጽ፣ በፅድቅ ሥራቸዉ ኹሉ ለሕዝበ ክርስቲያኑ አራያ በመሆን የክርስትና ሃይማኖት እንዲከበር፣ እንዲስፋፋና እንዲጠናቀር በማድረግ በፍፁም ተጋድሎ ቤተክርስቲያንን ያገለግሉ ስለሆነ የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዉለታቸዉን ባለመዘንጋት የቅድስና ማዕረግ ሰጥታ ትጠራቸዋለች፡፡ ስለነዚህ ቅዱሳን ነገስታት በገድላቸዉ፣በታሪክ ነገስታቸዉና በስንክሳር ከተዘገበዉ ሌላ ትተውልን የኼዱት አስደናቂ ቅርሶቻቸዉ ማንነታቸውን ይነግሩናል፡፡ በይተለይ በነዚህ ቅዱሳን የታነፁ አብያተ ክርስቲያናት ዓለም አቀፋዊ ዕውቅና ያገኙና መንፈሳዊ ምግባራቸዉንና የቅድስና ሕይወታቸውን አጉልተዉ በማሳየት አራያ የሚሆኑን ናቸዉ፡፡ (የቤተ ክርስቲያን ታሪክ፤ ክፍል-2 ገጽ 43)

የአራቱን ቅዱሳን ነገስታት ዘመነ መንግሥት ልዩ የሚያደርገዉ ከሁሉም በላይ ቤተክርስቲያን የነበራት ክብርና ድጋፍነበር፡፡ ነገስታቱ ራሳቸዉ ካህናት ፍፁም መንፈሳዊያን ስለነበሩ ለቤተክርስቲያን በነበራቸዉ ታላቅ ፍቅር ሌላዉም ህዝበ ክርስቲያን አርአያነቱን በመከተል ለቤተክርስቲያን ትልቅ ድጋፍ ነበረዉ፡፡እነዚህ ነገስታት አብያተ ክርስቲያናትን ከማሳነጽ ሌላ ለበርካታ ገዳማትና አድባራት ተጨማሪ መተዳደሪያ